የኢራንን ጦርነት ተቃውመው ከሥልጣናቸው የለቀቁት የአሜሪካ ባለሥልጣን በኤፍቢአይ እየተመረመሩ ነዉ

Date:

የኢራንን ጦርነት ተቃውመው ከሥልጣናቸው የለቀቁት የአሜሪካ ብሔራዊ የፀረ ሽብር ማዕከል የቀድሞ ዳይሬክተር ጆ ኬንት፤ በኤፍቢአይ ምርመራ እየተካሄደባቸው እንደሆነ ተገለጸ።

ምርመራው ምሥጢራዊ መረጃዎችን ለተለያዩ ምንጮች አሹልከዋል በሚል የተከፈተ እንደሆነ በአሜሪካ የቢቢሲ አጋር የሆነው ሲቢኤስ ኒውስ ለጉዳዩ ቅርበው ያላቸውን ምንጮችን ጠቅሶ ባወጣው ዘገባ ያሳያል።

በኤፍቢአይ የወንጀል ክፍል የተያዘው ይህ ምርመራ ባለሥልጣኑ ከኃላፊነት ከመልቀቃቸው አስቀድሞ የተጀመረ እና ለተወሰነ ጊዜ ሲካሄድ የቆየ መሆኑን ምንጮች ተናግረዋል ተብሏል።

የቀድሞው የፀረ ሽብር ኃላፊ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ከኃላፊነታቸው የለቀቁት ኢራን “ምንም ድርስ አደጋ” አልደቀነችም እንዲሁም “ጦርነቱ የተጀመረው በእስራኤል እና ጉልበት ባላቸው የአሜሪካ የውትትወታ ተቋማት ግፊት ነው” በሚል ነበር።

ረቡዕ ዕለት ከወግ አጥባቂው የፖለቲካ አስተያት ሰጪ ታከር ካርልሰን ጋር በነበራቸው ቃለ መጠይቅ ደግሞ፤ የኢራኑ ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ መገደላቸውን ተቃውመዋል። ኻሜኒን መግደል አሜሪካ ልትወስድ ከምትችላቸው እርምጃዎች መካከል “የመጨረሻ” መሆን እንደነበረበት ተናግረዋል።

“የኒውክሌር ፕሮግራማቸውን እያለዘበ ነበር፤ የኒውክሌር መሳሪያ እንዳያገኙ እየተከላከላቸው ነበር” ብለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...