የኢራንን ጦርነት ተቃውመው ከሥልጣናቸው የለቀቁት የአሜሪካ ባለሥልጣን በኤፍቢአይ እየተመረመሩ ነዉ

Date:

የኢራንን ጦርነት ተቃውመው ከሥልጣናቸው የለቀቁት የአሜሪካ ብሔራዊ የፀረ ሽብር ማዕከል የቀድሞ ዳይሬክተር ጆ ኬንት፤ በኤፍቢአይ ምርመራ እየተካሄደባቸው እንደሆነ ተገለጸ።

ምርመራው ምሥጢራዊ መረጃዎችን ለተለያዩ ምንጮች አሹልከዋል በሚል የተከፈተ እንደሆነ በአሜሪካ የቢቢሲ አጋር የሆነው ሲቢኤስ ኒውስ ለጉዳዩ ቅርበው ያላቸውን ምንጮችን ጠቅሶ ባወጣው ዘገባ ያሳያል።

በኤፍቢአይ የወንጀል ክፍል የተያዘው ይህ ምርመራ ባለሥልጣኑ ከኃላፊነት ከመልቀቃቸው አስቀድሞ የተጀመረ እና ለተወሰነ ጊዜ ሲካሄድ የቆየ መሆኑን ምንጮች ተናግረዋል ተብሏል።

የቀድሞው የፀረ ሽብር ኃላፊ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ከኃላፊነታቸው የለቀቁት ኢራን “ምንም ድርስ አደጋ” አልደቀነችም እንዲሁም “ጦርነቱ የተጀመረው በእስራኤል እና ጉልበት ባላቸው የአሜሪካ የውትትወታ ተቋማት ግፊት ነው” በሚል ነበር።

ረቡዕ ዕለት ከወግ አጥባቂው የፖለቲካ አስተያት ሰጪ ታከር ካርልሰን ጋር በነበራቸው ቃለ መጠይቅ ደግሞ፤ የኢራኑ ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ መገደላቸውን ተቃውመዋል። ኻሜኒን መግደል አሜሪካ ልትወስድ ከምትችላቸው እርምጃዎች መካከል “የመጨረሻ” መሆን እንደነበረበት ተናግረዋል።

“የኒውክሌር ፕሮግራማቸውን እያለዘበ ነበር፤ የኒውክሌር መሳሪያ እንዳያገኙ እየተከላከላቸው ነበር” ብለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአሜሪካ ጦር እስራኤልን ከኢራን መከላከሌን ላቆም እችላለሁ አለ

በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት በከፍተኛ ሁኔታ በናረበት በዚህ...

በፌደራሉ ሠራዊት እና በትግራይ ኃይሎች መካከል ግጭት መቀስቀሱ ተገለጸ

ከሱዳን ጋር በሚዋሰነው የሰሜናዊ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍል ውስጥ በሚገኝ...

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...