ፊፋ የኢራንን ጥያቄ ውድቅ አደረገ

Date:

ይህ ጥያቄ የቀረበው የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቡድኑን ደህንነት በተመለከተ በሰጡት አስተያየት እና በሁለቱ ሃገራት መካከል ያለው ውጥረት በመጨመሩ ምክንያት የኢራን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጨዋታዎቹ ወደ ሜክሲኮ እንዲዛወሩ በመጠየቁ ነው።

ፊፋ ባወጣው መግለጫ ሁሉም ተሳታፊ ሃገራት አስቀድሞ በወጣው የጨዋታ መርሃ ግብር መሰረት በተመደቡባቸው ከተሞች ጨዋታቸውን እንደሚያደርጉ በማሳወቅ ኢራን በአሜሪካ የምታደርጋቸው ጨዋታዎች እንደማይቀየሩ አረጋግጧል።

ኢራን በምድብ ጨዋታዎቿ ሰኔ 9 ቀን (June 15, 2026) ከኒውዚላንድ እንዲሁም ሰኔ 15 ቀን (June 21, 2026) ከቤልጂየም ጋር በሎስ አንጀለስ የምትጫወት ሲሆን የመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋን ሰኔ 20 ቀን (June 26, 2026) በሴያትል ከግብፅ ጋር ለማድረግ ተመድባለች።

ምንም እንኳን የኢራን ስፖርት ሚኒስቴር ከውድድሩ የመውጣት ፍንጭ ቢሰጡም የኢራን እግር ኳስ ፌዴሬሽን እና የእስያ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ግን ቡድኑ አሁንም በውድድሩ ላይ እንደሚሳተፍ ገልጸዋል። ኢራን ከውድድሩ የምትወጣ ከሆነ በእርሷ ምትክ ለመሳተፍ እንደ ኢራቅ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ያሉ ሃገራት ከፍተኛ እድል እንዳላቸው ተጠቁሟል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...