“የመካከለኛው ምስራቅ ቀውስ ያሰጋኛል” አውሮፓ ህብረት

Date:


የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ኡርሱላ ቮን ዲዬር ሊየን የኢራኑን ጦርነት ለመቋጨት ድርድር እንደሚያስፈልግ አሳሰቡ።

የቀጠለው ጦርነት እጅጉን አሳስቦኛል ብለዋል ቮን ዲዬር ሊዬን።

በድርድር ላይ መሰረቱን ያደረገ ሰላም መምጣት እንዳለበት ያስገነዘቡት ሀላፊዋ የሆርሙዝ ሰርጥ ጉዳይ መፍትሄ ሊበጅለት እንደሚገባም አስጠንቅቀዋል።

ጦርነቱ ሲጠናቀቅ የአውሮፓ አገራት ሆርሙዝን በመጠበቁ ተልዕኮ ለመሳተፍ እና ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውንም በካንቤራ አውስትራሊያ ከጠቅላይ ሚኒስትረ አንቶኒ አልባኔዝ ጋር ሆነው ጠቁመዋል።

ጫናውን በነዳጅና ጋዝ እንዲሁም በንግድ ስራዎቻችን ላይ እያስተዋልን ነው ያሉ ሲሆን የከፋ ቀውስ ሳይፈጠር አማራጭ መፈለግ ወሳኝ እንደሆነም ተናግረዋል።

በህዝባችን እና በነዳጅ ዋጋ መጨመርም ፈተና ላይ ነን ብለዋል ቮን ዲዬር ሊዬን።

ሆርሙዝ ለአውሮፓ አጋሮች በዓለም ዙሪያ ቁልፍ የኢነርጂ አቅርቦት ሰርጥ መሆኑን እና ለበርካታ እንቀስቃሴዎች ሚናው የዋዛ አለመሆኑንም አስምረውበታል።

ዘገባው የቢቢሲ ነው።

NBC Ethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በአንድ ዓመት ውስጥ ቃል የተገቡ 417 የዓይን ብሌኖች ለሆስፒታሎች ተሰራጩ

​ የኢትዮጵያ የደምና ሕብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት በተጠናቀቀው የ2018 በጀት...

በኢትዮጵያ በውርስና ስጦታ ላይ አዲስ ታክስ ሊጣል ነው

በኢትዮጵያ በውርስና ስጦታ ላይ አዲስ ታክስ ሊጣል ነው በኢትዮጵያ...

ትምህርት ሚኒስቴር ለአዲሱ ዓመት 11 አዳዲስ የሙያ ትምህርት ዓይነቶችን ይፋ አደረገ

​የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ከክልል...

የአዲስ አበባ ጉዳይ በሌሎች አጀንዳዎች ላይ የሚካሄደውን ምክክር ጥላ አጥሎበታል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በ25ኛ ቀን ውሎው በሥራ ቡድን ደረጃ...