ቻይና “አደገኛው እና ኃላፊነት የጎደለው” የአሜሪካ እገዳ “ውጥረቱን ያባብሳል” ስትል አስጠነቀቀች

Date:

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሜሪካ ከትናንት ጀምሮ ተግባራዊ ማድረግ ጀመረችውን ወደ ኢራን ወደቦች የሚደረግ የጉዞ እገዳ “አደገኛ እና ኃላፊነት የጎደለው” በማለት አወገዘ።

ውጤት ያልተገኘበት የአሜሪካ እና ኢራን ንግግር ፓኪስታን ውስጥ ከተካሄደ ከአንድ ቀን በኋላ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ወደ ኢራን ወደቦች ጉዞ እንዳይደረግ ዘግቷል።

የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ጉኦ ጂያኩን፤ እገዳው “ውጥረቱን ከማባባስ እና ቀድሞውንም ደካማ የሆነውን የተኩስ አቁም ስምምነት ከመሸርሸር” ያለፈ ውጤት እንደማይኖረው አስጠንቅቀዋል።

“ይሄ አደገኛ እና ኃላፊነት የጎደለው ባሕሪ ነው” ሲሉ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል።

ቃል አቀባዩ አክለውም ቻይና ለኢራን አዲስ የአየር መከላከያ ስርዓት እያዘጋጀች ነው የሚሉ ዘገባዎች “ሙሉ በሙሉ ፈጠራ ናቸው” ሲሉ አስተባብለዋል።

ይህ ሪፖርት መውጣቱን ተከትሉ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ቻይና ለኢራን ወታደራዊ እገዛ የምታደርግ ከሆነ በምርቶቿ ላይ የ50 በመቶ ታሪፍ እንደሚጥሉ ዝተዋል።

“አሜሪካ በቻይና ላይ ተጨማሪ ታሪፍ ለመጣል ይህንን እንደ ምክንያት የምትጠቀም ከሆነ፤ ቻይና በእርግጠኝነት ቆራጥ የአጸፋ እርምጃዎችን ትወስዳለች” ብለዋል።

BBC

የፎቶው ባ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚያደርጉት ድርድር እስኪጠናቀቅ ድረስ የተኩስ አቁሙ መራዘሙን አስታወቁ

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፓኪስታን ጥያቄ መሠረት ከኢራን ጋር የገቡትንየተኩስ...

ለኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ የሚውል የ40 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ተፈቀደ

የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የልማት ክንፍ የሆነው ኢአይቢ ግሎባል (EIB...

ሃይንከን በአልኮል መጠኑ ጠንከር ያለ ቢራ ለኢትዮጵያ ገበያ አስተዋወቀ

ሃይንከን ኢትዮጵያ በእለም አቀፍ ደረጃ ዝነኛ የሆነውን ዴሰፔራዶስ (Desperados)...