በሱዳን ብሉ ናይል ግዛት ብቻ ከ12ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች አሉ

Date:



በሱዳን የሚገኘው የተመድ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት፣ በሱዳን ብሉ ናይል ግዛት ውስጥ ብቻ ከ12,000 በላይ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ይገኛሉ።

በአሁኑ ወቅት በሱዳን ውስጥ በአጠቃላይ 68,750 ኢትዮጵያውያን ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች እንደሚገኙ የተገለጸ ሲሆን፣ አብዛኞቹ (65 በመቶው) በገዳሪፍ ግዛት ውስጥ ይኖራሉ።

ይህ አሃዝ የወጣው በሱዳን ያለው የእርስ በርስ ግጭት በበረታበትና በድንበር አካባቢ የጸጥታ ስጋቶችና የፖለቲካ ውጥረቶች እየጨመሩ በመጡበት ወቅት ነው።

በሱዳን እየተካሄደ ያለው ጦርነት የስደተኞችን ሕይወት እጅግ አስቸጋሪ እያደረገው ሲሆን፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በተለይም የትግራይ ተወላጆች ለከፍተኛ የምግብና የመድኃኒት እጥረት መጋለጣቸው ተነግሯል።

በጦርነቱ ምክንያት ረድኤት ሰራተኞች ከአካባቢው መውጣታቸውና የረድኤት አቅርቦት መቋረጡ ስደተኞቹን ለከፋ አደጋ አጋልጧቸዋል። በዚህም ምክንያት ብዙዎቹ ስደተኞች በሕይወታቸው ላይ ከፍተኛ ስጋት እንደተጋረጠባቸው በመግለጽ፣ ዓለም አቀፍ ጣልቃ ገብነት እንዲደረግና ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ በተደጋጋሚ ድምጻቸውን እያሰሙ ይገኛሉ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...