ኖ ሞር’ ቴአትር በአሜሪካ ለታዳሚ ሊቀርብ ነው

Date:

በአገር ውስጥ መድረኮች በነበረው ቆይታ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈው ‘ኖ ሞር’ (No More) የተሰኘው ቴአትር፣ የባህር ማዶ ጉዞውን በመጀመር በአሜሪካ ዴንቨር ኮሎራዶ ለታዳሚ ሊቀርብ ነው።

ተውኔቱ “በደል የፈፀሙ ሰዎች ተገቢውን ምላሽ ሊያገኙ ይገባል” የሚል ጠንካራ ማህበራዊ መልዕክትን በአስቂኝ ዘውግ አዋህዶ የያዘ ስራ ነው።

ቴአትሩ በኢትዮጵያ ለእይታ በበቃበት ወቅት አራት ተዋንያንን እና ሦስት የቴክኒክ ባለሙያዎችን በማሳተፍ ጥራት ያለው ዝግጅት ማቅረቡ ይታወሳል።

ለኮሎራዶው ዝግጅት በተደረገው ማሻሻያ መሰረት ቴአትሩ የመጀመሪያ ተዋንያን ላይ መጠነኛ ለውጥ ተደርጓል።

‘ኖ ሞር’ በሰው ልጅ ግንኙነት ውስጥ የሚፈጠሩ በደሎችንና ለበደሎቹ የሚሰጡ ምላሾችን በትውፊትና በዘመናዊ የቴአትር አቀራረብ የሚተነትን ነው።

ስራው በዴንቨርና አካባቢው ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የጥበብ ጥምን ለማርካት ታስቦ የተዘጋጀ ሲሆን፥ በቅርቡም የመድረክ ቀኑና የትኬት ሽያጭ ዝርዝር ይፋ እንደሚደረግ ተገልጿል።

ይህ ዝግጅት የኢትዮጵያ ቴአትር ከሀገር ውስጥ አልፎ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያለውን ተቀባይነት ለማሳደግ ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሎ ይታመናል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...