ኢራን የኒውክሌር ቁጥጥር እንዲደረግ ባትስማማ ኖሮ ድርድር ሳይካሄድ ይቀር እንደነበር ትራምፕ ገለጹ

Date:

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ “ኢራን ሙሉ በሙሉ እና ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ የኒውክሌር ቁጥጥር እንዲደረግ ፈቅዳለች” አሉ።

ኢራን ዓለም አቀፍ የኒውክሌር ተቆጣጣሪዎች ወደ አገሪቱ እንዲገቡ ልትፈቅድ ነው መባሉን ብታስተባብልም፤ ትራምፕ “ለከፍተኛ ደረጃ የኒውክሌር ቁጥጥር ተስማምታለች” ብለዋል።

ይህ የኢራን ስምምነት “ለረዥም ጊዜ እና እስከ ወዲያኛው” እንደሚዘልቅ ጠቅሰው “የኒውክሌር ታማኝነትን የሚያረጋግጥ ነው” ሲሉ ተናግረዋል።

“ኢራን ለዚህ ባትስማማ ኖሮ ተጨማሪ ድርድሮች አይኖሩም ነበር” በማለት አክለዋል።

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢስማኤል ባጋይ ከሰዓታት በፊት ዓለም አቀፍ የኒውክሌር ተቆጣጣሪዎች ወደ አገሪቱ እንዲገቡ እና የደረሰውን ጉዳት እንዲመለከቱ አለመፈቀዱን ገልጸዋል።

የአሜሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ ኢራን ለኒውክሌር ተቆጣጣሪዎች ፈቃድ መስጠቷን ተናግረዋል።

ትራምፕ በትሩዝ ሶሻል የማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ “በዚህ እና በሌሎችም ኢራን ባቀረበቻቸው ስምምነቶች መነሻነት ነው የሆርሙዝ ወሽመጥ ተከፍቶ እንዲቀጥል እንዲሁም በባሕር መተላለፊያ ላይ ተጨማሪ ማዕቀብ እንዳይጣል የተስማማሁት” ብለዋል።

BBC

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመረጃ ነጻነት አዋጅን በሙሉ ድምፅ አጸደቀ

በምክር ቤቱ የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ እውነቱ...

በቬንዝዌላ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ የ32 ሰዎች ህይወት አልፏል

በቬንዙዌላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን 7.2 እና 7.5...

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ “ሉሲ” ላገኟት ፕሮፌሰር የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጠ

የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ፥...

የሳህለወርቅ ዘውዴ አዲሱ አለም አቀፍ ሹመት በተመድ ልዩ ተልእኮ ተሰጣቸው

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተመድ ዋና ፀሀፊ...