አሜሪካ እና እስራኤል ደቡብ ሊባኖስን ለአገሪቱ ጦር የማስረከብ ዕቅድ

Date:

አሜሪካ ድጋፏን በሰጠችው ዕቅድ መሠረት እስራኤል እና ሊባኖስ፤ የደቡብ ሊባኖስ አስተዳደርን ለአገሪቱ ጦር ለማስረከብ ማሰባቸውን ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘገበ።

ሮይተርስ ከፍተኛ የእስራኤል ባለሥልጣናት የሆኑ ምንጮቹን ጠቅሶ እንደዘገበው፤ በዚህ ዕቅድ ውስጥ የሚካተቱ የሊባኖስ ኃይሎች ከአሜሪካ ሥልጠና ይሰጣቸዋል።

ከሄዝቦላህ ጋር ግንኙነት እንደሌላቸው ለማረጋገጥም የደኅንነት ማጣራት ይደረጋል።

የዜና ወኪሉ የጠቀሳቸው ምንጮች እንዳሉት፤ በደቡብ ሊባኖስ ያሉ አካባቢዎች ለአገሪቱ ጦር ተላልፈው እስከሚሰጡ ድረስ እስራኤል ቀጣናውን እየተቆጣጠረች ትቆያለች።

አሜሪካ እና እስራኤል በይፋ አስተያየታቸውን አልሰጡም። እስራኤል እና ሊባኖስ ዛሬ ረቡዕ በዋሽንግተን ውይይት እያደረጉ ይገኛሉ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በቬንዝዌላ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ የ32 ሰዎች ህይወት አልፏል

በቬንዙዌላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን 7.2 እና 7.5...

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ “ሉሲ” ላገኟት ፕሮፌሰር የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጠ

የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ፥...

የሳህለወርቅ ዘውዴ አዲሱ አለም አቀፍ ሹመት በተመድ ልዩ ተልእኮ ተሰጣቸው

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተመድ ዋና ፀሀፊ...

በሳዑዲ በምሕረት የተለቀቁ 320 ኢትዮጵያውያን

በሳዑዲ አረቢያ የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምህረት አዋጅ ከተሰጣቸው 1...