በአዲስ አበባ ከ75 እስከ 80 በመቶ ታክስ አሰባሰብ ግምት ላይ የተመሰረተ እደሆነ ተገለጸ

Date:

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የገቢዎች ቢሮ  በከተማዋ ከ75 እስከ 80 በመቶ የታክስ አሰባሰብ ግምት ላይ የተመሰረተ እደሆነ ገልጿል፡፡

በቢሮው የታክስ ኦዲት ዳይረክተር አቶ ጌታቸዉ ግርማ፤ግብር ከፋዩ አሁን ላይ ግብሩን እየከፈለ ያለዉ የተደራጀ ሰነድ ይዞ ሳይሆን በግምት ነዉ ብለዋል፡፡

አቶ ጌታቸዉ  ብዙ ጊዜ ግምት ትክክል ሊሆን አይችልም ስለዚህም መንግስትንም  ሆነ ህዝብን ከህግ ውጭ የመጉዳትም የመጥቀምም አጋጣሚዎችን ሊፈጥር ይችላል ብለዋል፡፡

በአዲስ አበባም ሆነ የክልል የገቢዎች ቢሮዎችም አሁን ላይ የግብር የአሰባሰብ ስርዓታቸዉ፤በጥናት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን በግምት ላይ በመሆኑ ዘመናዊ የታክስ አሰባሰብ ስረአት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

በመሆኑም ሁሉም ዜጋ ግዴታዉን አዉቆ ህጋዊ ሃላፊነቱን የሚወጣበት ዘመናዊ የታክስ አሰባሰብ ስርዓት በመዘርጋት ላይ እንዳለ አቶ ጌታቸዉ ግርማ አስታዉቋል፡፡

መጋቢ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት በዛሬ ዕትሟ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ነሔሴ 16 2018 ዓ.ም ገበያ...

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ...