ኢትዮጵያ የተቀቀለ ስጋ በመላክ ከ28 ሚሊዮን ዶላር በላይ አገኘች

Date:

ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ወደ ቻይና እና ሞንጎሊያ ጥራቱና ደኅንነቱ የተረጋገጠ የተቀቀለ ሥጋ በመላክ ከ28 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቷን የኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣን አስታወቀ።

የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ድሪባ ኩማ እንደገለጹት፣ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከሚሌ ኳራንታይን 400 ሺህ የቁም እንስሳት ጤንነታቸው ተረጋግጦ በባለሥልጣኑ ሰርተፍኬት ወደ ውጭ ሀገር በመላክ ከ28 ሚሊዮን ዶላር በላይ ተገኝቷል።

በተለይም ኢትዮጵያ ለዓረብ ሀገራት ብቻ ስጋ ስትልክ የቆየች ሲሆን፣ በዚህ ዓመት ወደ ቻይና ስጋ መላክ መጀመሯ ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል።

በ2016 ዓ.ም. ዓመቱን ሙሉ 300 ሺህ ያህል ከብቶች ወደ ውጭ ተልከው 18 ሚሊዮን ዶላር ብቻ ተገኝቶ እንደነበር አስታውሰው፣ በዚህ ዓመት ግን በግማሽ ዓመት ውስጥ ከ400 ሺህ በላይ ከብቶች ተልከው ከ28 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን ከፕሬስ ድርጅት ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

ቅዳሜገበያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...