ባሳለፍነው እሁድ ሚያዝያ 12 ቀን 2017 በተከበረው የትንሳኤ በዓል ላይ ወደ 6 ሺሕ 500 እንስሳት ይታረዳሉ ተብሎ በእቅድ ተይዞ የነበረ ሲሆን፤ 5 ሺሕ 756 እንስሳት እንዲታረዱ ማድረጉን የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት አስታውቋልል
በዚህም ድርጅቱ የእቅዱን 86 ነጥብ 6 በመቶ ማከናወን መቻሉን የድርጅቱ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አታክልቲ ገብረሚካኤል ተናግረዋል።
ከእነዚህም ውስጥ 3 ሺ 200 የሚሆኑት የከብት ዘሮች ትላልቅ እንስሳት ሲሆኑ፤ እንደ በግና ፍየል አይነቶች ትናንሽ እንስሳት ደግሞ 2 ሺ 547 መሆናቸውን ገልጸዋል።
5 ሺ 756ቱም እንስሳት በዋናው የእንስሳት ማረጃ ቦታ “ቄራ” እና አቃቂ ቅርንጫፍ በሚገኘው በኩል በሁለቱም ቦታዎች እንዲታረዱ መደረጉንም አስታውቀዋል።
በድርጅቱ ሱቆች በኩል የሚደረጉ ግብይቶችን በተመለከተም ተመጣጣኝና የአገልግሎት ክፍያ ብቻ እንደሚያስከፍሉ አንስተዋል።
ለአብነትም አንድ በሬ ተመርምሮ፣ ታርዶ እና ታጥቦ ሲያበቃ ወደ ተጠቃሚው ለማድረስ 1 ሺሕ 457 ብር እንደሚያስከፍሉ ተናግረዋል።
በተደረገው ዝግጅት መሰረትም ምንም አይነት ችግር ሳይኖር ያለቅሬታ መስተናገዱን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው አክለዋል።
“በአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የታረዱ እንስሳትን ተረፈ ሥጋ ወደ ተረፈ ምርት የመቀየር ሥራ በጥሩ ሁኔታ ተከናውኗል” ሲሉም ገልጸዋል።
