ከውጭ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ተገዝቶ በሞጆ ደረቅ ወደብ አንድ ዓመት ከአራት ወራት መቆየቱ የሚነገርለት የመሮጫ መም (ትራክ)፣ በጊዜው ለታለመለት ጥቅም ባለመዋሉ ምክንያት በቆይታ ብዛት እየተበላሸ መሆኑ ተገለጸ፡፡ ለአዲስ አበባ ስታዲየም ተብሎ የተገዛው ይህ የመሮጫ መም ወደ አዲስ አበባ መጥቶ ለሚፈለገው አገልግሎት እንዳይውል ምክንያት ተብሎ እየተጠቀሰ የሚገኘው የስታዲየሙ የሳር ተከላ ሥራ በታቀደለት ጊዜና ወቅት ሊጠናቀቅ ባለመቻሉ ነው፡፡
አንጋፋው የአዲስ አበባ ስታዲየም ከአራት ዓመታት በፊት የዓለም አቀፉ እግር ኳስ ማኅበር (ፊፋ) ‹‹ዝቅተኛውን መሥፈርት አያሟልም›› በሚል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድኖች ማናቸውንም አኅጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ውድድሮችን እንዳያስተናግድ ማገዱ ይታወሳል፡፡ መንግሥት የደረጃ ማሻሻያ ግንባታው የዓለም አቀዱ የዕገዳ ውሳኔ ዕውን በሆነ ማግሥት ቢጀምረውም፣ እስካሁን ሊጠናቀቅ ባለመቻሉ ስታዲየሙ ከአገልግሎት ውጪ እንደሆነ ይገኛል፡፡
ሞጆ ደረቅ ወደብ ላይ የሚገኘውና ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የፈሰሰበት የመሮጫ መም እየተበላሸ መሆኑ ተገለጸ
Date:
