ቼልሲ ማንቼስተር ዩናይትድን አሸነፈ

Date:

በ37ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቼልሲ ማንቼስተር ዩናይትድን 1 ለ ዐ አሸንፏል።

የምዕራብ ለንደኑን ክለብ ቼልሲ ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ማርክ ኩኩሬያ በሁለተኛው አጋማሽ ከመረብ አሳርፏል።

ቼልሲ የምሽቱን ድል ተከትሎ ነጥቡን 66 በማድረስ በኒውካስል ዩናይትድ በግብ ክፍያ ተበልጦ 4ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል።

በውድድር አመቱ በፕሪሚየር ሊጉ ብቻ 18ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ማንቼስተር ዩናይትድ 16ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

ቀደም ብሎ ምሽት 3:30 በተደረገው ጨዋታ አስቶን ቪላ ቶተንሃም ሆትስፐርን 2 ለ 0 በማሸነፍ ለሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎ ወሳኝ 3 ነጥብ አሳክቷል።

የአስቶንቪላን ግቦች ኮንሳ እና ካማራ በሁለተኛው አጋማሽ ከመረብ አሳርፈዋል።

ቪላ ነጥቡን 66 በማድረስ በኒውካስል ዩናይትድና ቼልሲ በግብ ክፍያ ተበልጦ 5ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ፥ ሽንፈት ያስተናገደው ቶተንሃም በነበረበት 17ኛ ደረጃ ላይ ለመቆየት ተገዷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጥቃት አድራሹ ከካሊፎርኒያ መሆኑን ትራፕ ገለፁ

ትናንት ቅዳሜ ምሽት በዋይት ሃውስ የጋዜጠኞች ማኅበር የእራት ግብዣ...

በኬንያ የመንገደኞች አውሮፕላን ከመስመሩ ወጥቶ ተከሰከሰ

ዛሬ ረፋድ ላይ በኬንያ ማንዴራ የአውሮፕላን ማረፊያ አንድ...

አቶ ጀማል አህመድ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ተጨማሪ 26 ሚሊየን ብር ሰጡ

አቶ ጀማል አህመድ ባሳለፍነው ወር ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ  ከሰጠው...

“የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከል”በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሊከፈት ነው

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከቻይና-አፍሪካ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር "የቻይና-አፍሪካ የምርምር...