የደቡብ አፍሪካ መሪ ራማፎሳ ወደ አሜሪካ አቀኑ፤ ነገ ከትራምፕ ጋር ይገናኛሉ

Date:

የፕሬዝዳቱ ፅህፈት ቤት “የጉብኝቱ ዓላማ በአሜሪካና በደቡብ አፍሪካ መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ዳግም ማስተካከል እና ማነቃቃት ነው” ብሏል።

ጉብኝቱ በዋናነት የሁለትዮሽ፣ የኢኮኖሚ እና የንግድ ግንኙነቶችን እንደገና ማነፅ ላይ ያተኩራል።

አሜሪካ በአፍሪካነሮች (ነጭ ደቡብ አፍሪካውያን) ላይ ያነጣጠሩ የመሬት ወረራዎች ዙሪያ ባቀረበችው ክስ ምክንያት በአሜሪካ እና በደቡብ አፍሪካ መካከል ያለው ግንኙነት ተበላሽቷል። ትራምፕ “በዘር ላይ የተመሰረተ መድልዎ” ሰለባዎች ናቸው በማለት የአፍሪካነር “ስደተኞችን” አሜሪካ ውስጥ ለማስፈር በየካቲት ወር ትዕዛዝ ሰጥተዋል። ባለፈው ሰኞ የመጀመሪያው ቡድን አሜሪካ ደርሷል።

ፕሪቶሪያ ክሱን መሠረተ ቢስ እና ፖለቲካዊ ያለችው ሲሆን ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ምንም ዓይነት የዘር መድልዎ የለም ብላ ተከራክራለች።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...