በኢትዮጵያ ከልጅነት ጋብቻ ጋር በተገናኘ ለህልፈት የሚዳረጉ በርካታ ሴት ህፃናት መኖራቸው ተገለፀ

Date:

በኢትዮጵያ እድሜያቸው ከ18 አመት በታች የሆኑ ሴት ህፃናት ከልጅነት ጋብቻ ጋር በተያያዘ ለህልፈት እንደሚዳረጉ የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።

በሚኒስቴሩ የስነተዋልዶ ጤና ፣የቤተሰብ እቅድ፣የአፍላወጣቶችና ወጣቶች ፕሮግራም ሀላፊ ዶክተር አለማየሁ ሁንዱማ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት የስነተዋልዶ ጤናን ተደራሽ ለማድረግ የተለያዮ ስራዎች ተሰርተዋል።

ይህም የእናቶችን ሞት ለመቀነስ ጉልህ ሚና እንዳለው የተገለፀ ሲሆን አሁን ላይ ከልጅነት እርግዝና ጋር በተገናኘ በርካታ ሴት ህፃናት ለህልፈት እንደሚዳረጉ ተጠቅሷል።

በእዚህ የእድሜ ክልል ውስጥ እያሉ በጋብቻ በሚቆዮበት ወቅት ብዙ ቁጥር ያላቸውን ልጆች የመውለድ እድል ስላላቸው በወሊድ ጊዜ ለሞት ሊጋለጡ የሚችሉበት ሁኔታ መኖሩ ተገልጿል።

ይህም አዲስ አበባን እና ድሬደዋን ጨምሮ በሌሎች ስፍራዎች የሚታይ ነው ያሉት ሀላፊው በአርብቶ አደርና በከፊል አርብቶ አደር ቦታዎች ችግሩ በስፋት ይስተዋላል ብለዋል።

በኢትዮጵያ አሳሳቢ እየሆነ የመጣውን የልጅነት እርግዝናን ለመከላከል እስከ ፈረንጆቹ 2030 ድረስ የሚቆይ ፍኖተ ካርታ መዘጋጀቱን ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...