አንድ ሰው በህይወት ተገኝቷል -የሟቾች ቁጥር 290 ደረሰ

Date:

*በህንድ የአህመደዳብ ከተማ ፖሊስ ኮሚሽነር ቀደም ብለው በሰጡት መግለጫ፣ ከተከሰከሰው አውሮፕላን አንድም ሰው በህይወት የተረፈ እንደሌለ ቢናገሩም፣ አሁን ላይ ግን አንድ ሰው በህይወት መገኘቱን ለህንድ መገናኛ ብዙሃን አሳውቀዋል፡፡

*ከተረፉት ግለሰቦች አንዱ እንግሊዛዊ ሲሆን፤ ከአውሮፕላኑ ውስጥ በመስኮትበመዝለል በ”ተዓምር” ከሞት መትረፉ ተዘግቧል፡፡

“አውሮፕላኑ ከመሬት ከተነሳ 30 ሰከንዶች በኋላ ከባድ ድምጽ ተሰማ፤ ከዚያ አውሮፕላኑ ተከሰከሰ፤ ሁሉም ነገር በከፍተኛ ፍጥነት ነው የሆነው” – በህይወት የተረፈው እንግሊዛዊ

*በአውሮፕላኑ 169 ህንዳውያን፣53 እንግሊዛውያን፣ እንዲሁም 7 የፖርቱጋልና 1 የካናዳ ዜግነት ያላቸው ተሳፋሪዎች ነበሩ – የሕንድ አየር መንገድ

*የሟቾች ቁጥር 290 መድረሱ የተዘገበ ሲሆን፤ እስካሁን 204 አስከሬኖች መገኘታቸውን የፖሊስ ኮሚሽነሩ ገልጸዋል – ነገር ግን አውሮፕላኑ ሲከሰከስ ምን ያህሎቹ መሬት ላይ ወይም በአውሮፕላኑ ውስጥ እንደነበሩ አይታወቅም ብለዋል፡፡

*አውሮፕላኑ የተከሰከሰው በሃኪሞች ማረፊያ ቤት ላይ ነው – አንዲት እናት ወንድ ልጇ እንዴት ከሁለተኛ ፎቅ ላይ ዘሎ ህይወቱን እንዳተረፈ ለመገናኛ ብዙኃን ገልጻለች፡፡

*የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ በህንድ በደረሰው አሰቃቂ የአውሮፕላን አደጋ ልባቸው መሰበሩን ገልጸው፣ ለሟች ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝተዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...