አምባሳደሩ ከተዋጊዎቹ በኩል አወንታዊ ምላሽ መገኝቱን አስታወቁ

Date:

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ማሲንጋ በቅርቡ ከድሮን ጥቃት ጋር በተያያዘ ኤምባሲያቸው ያወጣው መግለጫ “በስህተት ነው” ሲሉ ገለጹ

በኢትዮጵያ የአሜሪካን አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ኤምባሲያቸው ግንቦት 15 ቀን 2017 ዓ.ም “የፌደሬል መንግስት በዜጎቹ ላይ የሚፈጽመውን የድሮን ጥቃት በአስቸኳይ እንዲያቆም” በሚል የተላለፈው መልዕክት በስህተት ነው ሲሉ ገለጹ፤ መልዕክቱ “በአስተዳደራዊ ስህተት” የተካተተ ነበር ሲሉ በምክንያትነት አስቀምጠዋል።

“ስህተት ነበር፤ ስህተት ነበር ከማለት ውጭ ምንም ተጨማሪ የሚገለጽም ይሁን የሚቀነስ ነገር የለውም በመጀመሪያ የተጻፈውን የመግለጫውን ረቂቅ ነበር የተጠቀሙት፤ እኔ ያላየሁት እና ያላፀደኩትን ነው የተጠቀሙት፤ ይህም በአስተዳደራዊ ችግር የተፈፀመ እና እንዳለመታደል ሁኖ ተላለፈ” ሲሉ ዛሬ ሰኔ 5 ቀን 2017 ዓ.ም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ተናግረዋል።

በመጀመሪያ ኤምባሲያቸው ያሰራጨው መረጃ “የፌደሬል መንግስት በዜጎቹ ላይ የሚፈጽመውን የድሮን ጥቃት በአስቸኳይ እንዲያቆም” የሚል ሀሳብ የነበረው ቢሆንም ከሰአታት በኋላ ይህ ሀሳብ እንዲነሳ ተደርጓል።

አምባሳደሩ በዛሬው መግለጫቸው በኤምባሲያቸው በኩል በኢትዮጵያ ለሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ሀይሎች ለቀረበው የሰላማዊ ውይይት ጥሪ አስመልክተው በሰጡት አስተያየት “ከተወሰኑ የኦሮሞ ነጻነት ተዋጊ ቡድኖች እና ከአንዳንድ የፋኖ ታጣቂ ቡድኖች” በኩል አወንታዊ ምላሽ ማግኘቱን እና ተስፋ እንዳላቸው አስታውቀዋል፤ “በእርግጥ ብዛት ያላቸው እና ዘርዘር ያሉ ቅድመ ሁኔታዎችን አቅርበዋል” ብለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...