እድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች ከሆነ ሕጻናት መካከል 40 በመቶ ያህሉ ለመቀንጨር ተጋልጠዋል

Date:

በአማራ ክልል ባለፉት ዓመታት በተከሰተው ግጭት፣ መፈናቀል እና የዝናብ እጥረት ምክንያት እድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች ከሆኑ ሕጻናት መካከል 40 በመቶ ያህሉ ለመቀንጨር ችግር መጋለጣቸው የክልሉ ጤና ቢሮ አስታውቋል።

በቢሮ የስርዓተ ምግብ የፕሮግራም አስተባባሪ ስሜነህ ወርቁ፤ “በተለይ የምስራቅ እና ምዕራብ አማራ አካባቢዎች የሚገኙ ሕጻናት ከፍተኛ ችግር ውስጥ ይገኛሉ” ሲሉ ተናግረዋል።

ችግሩን ለማቃለል ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን ከእርግዝና ክትትል ጀምሮ እናቶች እና ሕጻናት የተመጣጠነ ምግብ እና የሕክምና ክትትል ይደረግ እንደነበረ አስታውሰው፤ በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት እርዳታው እየቀነሰ መሆኑን ተናግረዋል።

የክልሉ የስርዓተ ምግብ የፕሮግራም አስተባባሪ አክለውም፤ ወላጆች ስለመቀንጨር ያላቸው ግንዛቤ አነስተኛ መሆኑ ችግሩን ካባባሱ ሰበቦች መሐከል አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

“ለክልሉ የሚመደበው የጤና በጀት አነስተኛ መሆኑ፣ በግጭት ምክንያት ጥቂት የማይባሉ የጤና ተቋማት ላይ ጉዳት መድረሱ፣ ደግሞ በፍጥነት የማስተካከያ እርምጃዎች መውሰድ እንዳይቻል አድርገዋል” ተብሏል፡፡

ahaduRadio

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...