ለ472 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ ተደረገ!

Date:

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለ472 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ። የክልሉ መንግሥት ከፊታችን የሚከበረውን 1 ሺህ 446ኛውን የዒድ አልፈጥር በዓል እና መጪውን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ ለ472 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉ ተገልጿል።

በወንጀል ጉዳይ እስራት ተፈርዶባቸው በማረሚያ ቤት ከሚገኙት ውስጥ ሕጉ የሚጠይቀውን መመዘኛ አሟልተው ለተገኙ በመደበኛ ለ459 ወንዶች እና ለ12 ሴቶች እንዲሁም በልዩ ሁኔታ ለ1 ሴት የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ ስለመደረጉ የክልሉ ርዕሰ መሥተዳደር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) መናገራቸውን የክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስፍሯል።

ይቅርታ ከተደረገላቸው ታራሚዎች መካከል፤ 471 በሙሉ ይቅርታ ከእስር እንዲለቀቁ መወሰኑም ተመላክቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በሱዳን ብሉ ናይል ግዛት ብቻ ከ12ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች አሉ

በሱዳን የሚገኘው የተመድ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን ይፋ ባደረገው መረጃ...

ትራምፕ አሜሪካ እና ኢራን “በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት ውስጥ” ሊወያዩ እንደሚችሉ ተናገሩ

ዶናልድ ትራምፕ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል “በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት...

የኢራን ጦርነት የሚቀጥል ከሆነ የዓለም ምጣኔ ኃብት አደጋ ላይ እንደሚወድቅ አይኤምኤፍ አስጠነቀቀ

የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) በመካከለኛው ምሥራቅ የሚካሄደው የኢራን...

የመምህር ዘላለም ወንድሙ (ወልደ ሰማዕት) የ፵ ቀን መታሰቢያ ጥሪ

​"የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው!" (ምሳሌ ፲፥፯)​በሕይወትና በቃል ትምህርታቸው ብዙዎችን...