የአሜሪካው የቴክኖሎጂ ኩባንያ ማይክሮሶፍትመቀመጫቸውን ቻይና ባደረጉ መረጃ መንታፊዎች ጥቃት ተፈጽሞብኛል አለ።
የኩባንያው የሶፍትዌር ሰርቨር እና የቢዝነስ ዳታው በመረጃ መንታፊዎቹ እንደተመዘበረበት
ገልጿል።
በዚህ የመረጃ ምንተፋ ሦስት የቻይና ኩባንያዎች የተሳተፉ ሲሆን፥ ሁለቱ በመንግስትየሚደገፉ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች መሆናቸውንም ነው ኩባንያው የገለጸው።
በዋናነትም ሼርፖይንት የተባለውንና በተቋማት የኮምፒውተር ኔትወርክ ሲስተምን
እርስ በእርስ ለማገናኘትና የመረጃ ማጋሪያ ስርአቶች ለመስራት የሚያገለግለው ሰርቨር ላይ የመረጃ ምዝበራ አድርገዋልም ነው ያለው።
አሁን ላይ ከመረጃ ምንተፋው ጋር በተያያዘ ማጣራት እያደረኩ ነው ያለው ኩባንያውለደንበኞቹም የማስጠንቀቂያ መልዕክት ልኳል።
