“ስምምነት ላይ አልተደረሰም ግን ተስፋ ሰጪ ነው” ፑቲንና ትራምፕ

Date:

አለም በጉጉት ሲጠብቀው የነበረው የፑቲንና የትራምፕ ውይይት ያለ ስምምነት ቢጠናቀቅም  ተስፋ ሰጪ እንደነበር መሪዎቹ ገልጸዋል ።

ትራምፕ ከፑቲን ጋር የካሄዱትን የመሪዎች ስብሰባ ከ0 እስከ 10 ባለው ሚዛን “አስር” እንደሚሰጡት ተናግረዋል
ትራምፕ ከፑቲን ጋር ባደረጉት ውይይት ከፍተኛ መሻሻል ታይቷል ብለዋል።

ዩክሬንን በተመለከተ ብዙ ነጥቦች ላይ እንደተስማሙና በቀሪዎቹ ጉዳዮች ዙሪያ ለመስማማት ጥሩ እድሎች መፈጠራቸውን ተናግረዋል።

ትራምፕ በዩክሬን ጉዳይ ከፑቲን ጋር የተደረሰውን መግባቢያ የመጨረሻ ስምምነት እንዳልሆነና መጀመሪያ የሁሉም ወገኖች ስምምነት እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል።

ፑቲን እና ትራምፕ  ለ10 ደቂቃ ያህል መድረክ ላይ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በግል  በነበራቸው ቆይታ  ላይ ለውጦች መኖራቸውን ይፋ አድርገዋል።

ፕሬዚዳንቶቹ ለውጦች ተመዝግበዋል ቢሉም “የዩክሬኑን ጦርነት መቋጨት” በሚለው ጉዳይ ላይ ግን ያለ ምንም መስማማት ተለያይተዋል።

ፑቲን አስፈሪውን ጦርነት የመቋጨት ፍላጎቱ እንዳላቸው ቢያሳውቁም ለጦርነቱ መንስዔ የሆኑ ጉዳዮች ሁሉ ከስር መሰረቱ መላ ሊበጅላቸው ይገባል የሚል አቋም አላቸው።

ዩክሬን እና አውሮፓውያን በንግግሮች ላይ አሻጥርራቸውን ማቆም እንዳለባቸውም ቭማድሚር ፑቲን አሳስበዋል።

ዶናልድ ትራምፕ ቀጣይ ወደ ሞስኮ ሊያቀኑ እንደሚችሉም ፑቲን ሀሳብ ሰተዋል።

ከስድስት እስከ ሰባት ሰዓታት ይወያያሉ የተባሉት ፑቲንና ትራምፕ ሶስት ሰዓታት እንኳን ሳያወሩ ስብሰባቸውን አጠናቀዋል።

ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ጋር በአላስካ ካደረጉት ውይይት በኋላ ትራምፕ ለፎክስ ኒውስ በሰጡት አስተያየት፤ በብዙ ነጥቦች ላይ ተስማምተናል ብለዋል።

ትራምፕ ከፑቲን ጋር የነበራቸው ግኑኝነት በጣም ጥሩ በመሆኑ ለተጨማሪ 2-3 ሳምንታት ስለ አዲስ የሁለተኛ ደረጃ ማዕቀብ እንደማያስቡ ገልፀዋል።

ትራምፕ “ስምምነት ፍጠር ይገባል። ሩሲያ በጣም ትልቅ ኃይል ነች” ብለዋል ሲል  ስፑትኒክ ዘግቧል ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...