” በህዳሴ ላይ አንድም ብር እርዳታ፣ አንድም ብር ብድር ኢትዮጵያ አልወሰደችም ” – ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Date:


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ከፓርላማ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት፣ ” በህዳሴ ላይ አንድም ብር እርዳታ፣ አንድም ብር ብድር ኢትዮጵያ አልወሰደችም ” ሲሉ ግልጽ ምላሽ ሰጥተዋል።

” በጀግኖች ኢትዮጵያውያን ቁርጠኛ አቋም በሀገር ውስም በከሀገር ውጭም ያሉ ኢትዮጵያውያን በቁርጠኝነት ጨከሰነው በጋራ ቆመው ስለሰሩ የተከወነ ፕሮጀክት ነው ” ሲሉም ተናግረዋል።

ዐቢይ (ዶ/ር) ይህን ያሉት ሜጋ ፕሮጀክቶች እምብዛም ስለሌሉ ወጣቶች ለስራ አጥነት ጨምር እየተጋለጡ በመሆኑ ለዚሁ ምላሽ እንዲጠሱ ከፓርላማ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ ሲሰጡ ሲሆን፣ ” ከዚህ ንግግራቸው አስከትለውም፣ ” ግን በዚህ አላበቃም፤ ህዳሴ ከአፍሪካ አንደኛውን ሰርተናልና ሌላ አያስፈልግም እኮ አላለችም ኢትዮጵያ ” ብለዋል።

” በአፍሪካ ሦስተኛውንም ኮይሻ እየገነባን ነው ያለነው። የንፋሱን ሳንጨምር። በርካታ ፕሮጀክቶች ይሰራሉ ” ነው ያሉት።

” ‘ፕሮጀክቶ ቋሟል፤ ሜጋ፣ ሜጋ ፕሮጀክት የለም’ ለተባለው። እውነት ነው ፕሮጀክት የለም። ግን ከአፍሪካ አንደኛው ኤርፓርት ኢትዮጵያ ውስጥ ተጀምሯል። እንደዚህ ያለ ፕሮጀክት ኢትዮጵያ አስባም ሰርታም አታውቅም” ሲሉ መልሰዋል።

” እውነት ነው ፕሮጀክት ቀንሷል የማዳበሪያ ፋብሪካ ኢትዮጵያ ውስጥ ተጀምሯል። ፕሮጀክት ቀንሷል የጋዝ ፌዝ ዋን ጨርሰን ፌዝ ቱ እና ሪፋይነሪ እየሰራን ነው ” ሲሉ በርካታ ግዙፍ ግዙፍ ፕሮጀክቶች እየተሰሩ መሆኑን አሳውቀዋል።

” በሜጋ ፕሮጀክት ፣ በፕሮጀክት ክትትል ፣ በፕሮጀክት አፈጻጸም ፣ በፕሮጀክት አመራር እንኳን ኢትዮጵያ ውስጥ ድፍን አፍሪካ ገና ከኢትዮጵያ ይማራል ” ብለዋል።

” ሰባት ቀን ቀን እና ማታ በየጥሻው ውስጥ የምንዞረው ፕሮጀክት ተጀምሮ ሳያልቅ እንዳይቆም ነው ” ሲሉ ተናግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...