በሆንግ ኮንግ በተከሰተ የእሳት አደጋ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 55 ደርሷል

Date:

በሆንግ ኮንግ ታይ ፖ አውራጃ ውስጥ በሕዝብ መኖሪያ ቤቶች ላይ በደረሰ ከባድ የእሳት አደጋ ቢያንስ 55 ሰዎች ህይወታቸው እንዳለፈ እና ከ270 በላይ የሚሆኑት ደግሞ የደረሱበት አለመታወቁን የሀገሪቱ ባለስልጣናት አስታውቀዋል፡፡

ባለሥልጣናቱ እንዳሉት በእሳት ከተያያዙት ሰባት ሕንፃዎች ውስጥ አራቱን መቆጣጠር እንደተቻለ እና የቀረቱን ህንፃዎች ደግሞ እስከ ምሽት ድረስ ለማጥፋት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

እሳቱ እየቀነሰ በመጣ ቁጥርም እሳቱ መጀመሪያ እንዴት ሊነሳ ቻለ? እና ተጠያቂው ማን መሆን አለበት? የሚሉ ጥያቄዎች እየተበራከቱ እንደመጡ ተነገሯል፡፡

እሳቱ በፍጥነት እንዲስፋፋ አድርገዋል ተብለው ከተጠረጠሩ ተቀጣጣይ ነገሮች ጋር በተያያዘም በግድያ ወንጀል ተጠርጥረው ሦስት የግንባታ ኩባንያ ሥራ አስፈጻሚዎች በፖሊስ መያዛቸው ተገልጿል፡፡

የእሳት አደጋ ሠራተኞች አሁንም እሳቱን ላማጥፋት ከፍተኛ ጥረት ይያደረጉ ይገኛሉ ሲል ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...