በምሥራቅ አፍሪካ የሚስተዋሉ ሽብርተኝነትንና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን ለመከላከል የቀጣናው ሀገራት የመረጃ ትብብር ወሳኝ ነው

Date:

በምሥራቅ አፍሪካ የሚስተዋሉ ሽብርተኝነትንና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን ለመከላከል የቀጣናው ሀገራት የመረጃ ትብብር ወሳኝ መሆኑን የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ታዜር ገብረእግዚአብሔር ገለጹ።

የአፍሪካ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት ኮሚቴ የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ስብሰባ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።

የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ታዜር ገብረእግዚአብሔር በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ በመረጃ ትብብር የቀጣናውን ደህንነት ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ይመክራል።

ሽብርተኝነት፣ ጽንፈኝነት እና ሌሎች ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ዛሬም ድረስ የምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና ስጋት ሆነው መቀጠላቸውን ገልጸዋል።

በመሆኑም በቀጣናው ያለውን የደህንነት ስጋት በመቆጣጠር ሰላም ለማስፈን በሀገራት መካከል የተቀናጀ የመረጃ ትብብር ያስፈልጋል ብለዋል።

የምሥራቅ አፍሪካ የመረጃና ደህንነት ተቋማት ስብሰባ፥ ቀጣናዊ ትብብሩ በተግባር የሚፈጸምበትን እድል እንደሚፈጥር ተናግረዋል።

የጸጥታ ስራ የጋራ ትብብርን የሚጠይቅ ነው ያሉት አቶ ታዜር፤ ተቋማቱ ፈጠራን የተከተለና የህግ ማዕቀፍን ታሳቢ ያደረገ ቅንጅት መፍጠር አለባቸው ብለዋል።

የአፍሪካ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት ኮሚቴ ዋና ፀሐፊ ጃክሰን ሀማታ በበኩላቸው፣ የአፍሪካ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት ኮሚቴ ዓላማው የቀጣናውን ደህንነት በጋራ ለመጠበቅ ትብብርን መፍጠር መሆኑን ገልጸዋል።

የምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት በመረጃ ላይ የተመሰረተ ቅንጅት በመፍጠር ሽብርተኝነትንና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን መከላከል እንዳለባቸው ተናግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...