በሳይበር ጥቃት ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አምስተኛ መሆኗ ተሰማ

Date:

ኢትዮጵያ በሳይበር ተጋላጭነት ከአፍሪካ አገራት 5ኛ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ የኢንተርፖል አዲስ ሪፖርት አመለከተ።

በአህጉሪቱ አጠቃላይ ከታዩ የዲጂታል ጥቃት ተጋላጭነቶች መካከል ኢትዮጵያ 3.3 በመቶ ድርሻ እንዳላት የተገለጸ ሲሆን፣ ፈጣን የቴክኖሎጂ እድገት ጉዞ ከሳይበር ደኅንነት መከላከያ አቅም እና ተቋማዊ ዝግጁነት ቀድመው መሄዳቸው ለዚህ ተጋላጭነት እንደዳረገው ሪፖርቱ አጋልጧል።

በአህጉሪቱ በሳይበር ጥቃት ሳቢያ የሚገጥመው አጠቃላይ ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ 5 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን የጠቆመው ድርጅቱ፣ አገራትና ድርጅቶች ለሳይበር ደኅንነት የሚያወጡት ወጪ ከ15 ቢሊዮን ዶላር በላይ ማሻቀቡን አመልክቷል።

በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ አገራት ላይ የሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች በሞባይል ገንዘብ ማጭበርበር፣ በቴሌኮሙኒኬሽን መሠረተ ልማቶች እና በወሳኝ ተቋማት ላይ ያተኮሩ መሆናቸው ተመላክቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኢትዮጵያዊዉ የመጀመሪያው የአይን ሐኪም ዶክተር ጳውሎስ አረፉ

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የዓይን ሐኪም እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዓይን...

ኢትዮጵያውያን ታዳጊዎች በዓለም አቀፍ የሮቦቲክስ ውድድር 3ኛ ወጡ

በካናዳ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የሮቦቲክስ ውድድር ላይ የተሳተፉት የኢትዮ...

ሁቲዎች የሳዑዲ የነዳጅ ማጣሪያ ላይ ጥቃት መፈፀማቸውን ገለጹ

የኢራን አጋር የሆኑት ሁቲዎች የሳዑዲ አራምኮ ጃዛን ነዳጅ ማጣሪያን...

በዓለም ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና ኢትዮጵያ 2ኛ የወርቅ ሜዳሊያ አገኝች

በሴቶች 3 ሺህ ሜትር የተወዳደሩት  ዮርዳኖስ ጽጋብ እና ሽቶ...