20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የሴቶች 5ሺ ሜትር በሁለት ምድብ የማጣሪያ ውድድር ተካሂዷል ።
በውድድሩ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች
አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ፤ አትሌት መዲና ኢሳ እና አትሌት ፋንታዬ በላይነህ ለፍፃሜ አልፈዋል።
በምድብ ሁለት የተወዳደሩት አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ አንደኛ ፤ መዲና ኢሳ 5ኛ ደረጃን በመያዝ ወደ ፍፃሜ አልፈዋል።
በመጀመሪያ ምድብ የተወዳደረችው አትሌት ፋንታዬ በላይነህ 6ኛ በመውጣት ለፍፃሜ አልፋለች።
አትሌት ብርቄ ሃየሎም ከምድቧ 9ኛ በመውጣት ወደ ፍፃሜ ለማለፍ ያደረገችው ጥረት ሳይሳካ ቀርተዋል።
የፍፃሜ ውድድሩ ቅዳሜ ከቀኑ 9:27 ይካሄዳል ።
