በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ዳግም ጦርነትእንዳይቀሰቀስ ዲፕሎማቶች አሳሰቡ

Date:

በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ዳግም ጦርነት እንዳይቀሰቀስ ከወዲሁ መግታት እንደሚገባ የአሜሪካና አውሮፓ ዲፕሎማቶች አሳሰቡ፡፡

የአፍሪካ ቀንድ ምክትል ልዩ መልዕክተኛ የነበሩት ፓይተን ኖፍ እና የቀይ ባህር የጥናት ማዕከል ሊቀመንበር አሌክሳንደር ሮንዶስ፣ በሁለቱ ጎረቤት ሀገራት መካከል የሚስተዋለውን ውጥረት አስመልክተው፣ ፎሬይን ፖሊሲ መጽሔት ላይ ሀሳባቸውን አጋርተዋል፡፡

በሁለቱም በኩል የሚስተዋሉ የቃላት ልውውጦችና የጦርነት ዝግጅቶች በሀገራቱ መካከል ጦርነት ሊቀሰቀስ እንደሚችል አመላካች እንደሆኑ ዲፕሎማቶቹ ጠቁመዋል፡፡

በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ያለው ፍጥጫ ወደ ጦርነት የሚያድግ ከሆነ ሰሜን ምስራቅ አፍሪካንና በጂኦፖለቲካዊ ጠቀሜታው ወሳኝ የሆነው ቀይ ባህር ላይም ችግር ሊጋርጥ እንደሚችል አመልክተዋል፡፡

አለም በሰፊ አህጉራዊና አለምአቀፋዊ ስርዓት አልበኝነት እየተናጠች በምትገኝበት በዚህ ወቅት፣ በትግራይ ያለው የፖለቲካና የጸጥታ ሁኔታ መበላሸት በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ጦርነትን ሊያስከትል እንደሚችልም አሳስበዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት በዛሬ ዕትሟ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ነሔሴ 16 2018 ዓ.ም ገበያ...

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ...