በዲጂታል ምህዳሩ የሚፈጸሙ ማጭበርበሮች 180 በመቶ ጨምረዋል

Date:

የማንነት ማረጋገጫና የኮምፒሊያንስ አገልግሎቶችን የሚሰጠው Sumsub የተባለዉ  ዓለማቀፍ ኩባንያ  አዲስ ባወጣው የማንነት ማጭበርበር ሪፖርቱ መሰረት፣ ምንም እንኳን ዓለም አቀፍ የማጭበርበር ሙከራዎች አጠቃላይ መቀዛቀዝ ቢያሳዩም፣ የሳይበር ወንጀለኞች ሰዉ ሰራሸ አስተዉሎትን (AI) በመጠቀም የሚሰነዘሩት የማጭበርበር ጥቃቶች በከፍተኛ ደረጃ እያደጉ መጥተዋል፡፡

እ.ኤ.አ በ2025 አጠቃላይ የማንነት ማጭበርበር ሙከራዎች መጠነኛ ቅናሽ (ከ2.6% ወደ 2.2%) ቢያሳዩም፣ በሰዉ ሰራሽ አስተዉሎትና በጥልቅ ማታለል (deepfake) የሚሰሩ እጅግ የተራቀቁ የማጭበርበር ሙከራዎች 180 በመቶ መጨመራቸዉን ሪፖርቱ አመልክቷል።

ሪፖርቱ፤ የተረጋጉ የሚመስሉ አጠቃላይ የጥቃት መጠኖች አደጋውን የሚደብቁ መሆኑንና እያንዳንዱ ስኬታማ የማጭበርበር ሙከራ አሁን ላይ ከፍተኛ ጉዳትና ረጅም ጊዜ የሚቆይ ተጽዕኖ እንደሚያስከትል ማስጠንቀቁን የINSA ዲጂታል መረጃ ጠቁሟል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...