የማንነት ማረጋገጫና የኮምፒሊያንስ አገልግሎቶችን የሚሰጠው Sumsub የተባለዉ ዓለማቀፍ ኩባንያ አዲስ ባወጣው የማንነት ማጭበርበር ሪፖርቱ መሰረት፣ ምንም እንኳን ዓለም አቀፍ የማጭበርበር ሙከራዎች አጠቃላይ መቀዛቀዝ ቢያሳዩም፣ የሳይበር ወንጀለኞች ሰዉ ሰራሸ አስተዉሎትን (AI) በመጠቀም የሚሰነዘሩት የማጭበርበር ጥቃቶች በከፍተኛ ደረጃ እያደጉ መጥተዋል፡፡
እ.ኤ.አ በ2025 አጠቃላይ የማንነት ማጭበርበር ሙከራዎች መጠነኛ ቅናሽ (ከ2.6% ወደ 2.2%) ቢያሳዩም፣ በሰዉ ሰራሽ አስተዉሎትና በጥልቅ ማታለል (deepfake) የሚሰሩ እጅግ የተራቀቁ የማጭበርበር ሙከራዎች 180 በመቶ መጨመራቸዉን ሪፖርቱ አመልክቷል።
ሪፖርቱ፤ የተረጋጉ የሚመስሉ አጠቃላይ የጥቃት መጠኖች አደጋውን የሚደብቁ መሆኑንና እያንዳንዱ ስኬታማ የማጭበርበር ሙከራ አሁን ላይ ከፍተኛ ጉዳትና ረጅም ጊዜ የሚቆይ ተጽዕኖ እንደሚያስከትል ማስጠንቀቁን የINSA ዲጂታል መረጃ ጠቁሟል፡፡
