ቤተክርስቲያኗ በፒያሳና አራት ኪሎ ሁለት ሕንጻዎች ልትገነባ ነው

Date:

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በፒያሳና አራት ኪሎ ለምታስገነባቸው ሕንጻዎች የሳይት ርክክብ ተደረገ።

ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በፒያሳና በአራት ኪሎ የሚገነቡትን የቤተክርስቲያኗን ሕንጻዎች በጨረታ ላሸነፉ ኮንትራክተሮች ሳይተቶቹን አስረክዋል።

በዛሬው ዕለት ርክክብ የተደረገላቸው ሳይቶች ፒያሳ አካባቢ የሚገነባው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ዝክረ ቅዱሳን ህንጻ G+7አንዱ ሲሆን የግንባታ ሥራውን ለማከናወን ምንሀር ኮንስትራክሽን የተባለው ሕንጻ ተቋራጭ አሸንፎ ሳይቱን የተረከበ ሲሆን አራት ኪሎ አካባቢ ከጠቅላይ ቤተክህነት ጀርባ ባለው ስድስት ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ሕንጻ አበው በሚል ስያሜ ለሚገነባው B3+G+12 ሁለገብ ሕንጻ ደግሞ አተም ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ የተባለው ኮንትራክተር አሸናፊ በመሆን ሳይቱን ተረክቧል።

በሁለቱ ቦታዎች የሚገነቡት ሕንጻዎች ማለትም በአራት ኪሎ አካባቢ የሚገነባው ሕንጻ በሰላሳ ወራት፣ ፒያሳ አካባቢ የሚገነባው ሕንጻ ደግሞ በሃያ ወራት ውውጥ ተገንብተው የሚጠናቀቁና አገልግሎት ላይ የሚውሉ መሆናቸው ታውቋል።

በሳይት ርክክቡ ወቅት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት፤ “ቤተክርስቲያን የምታስገነባቸውን ሕንጻዎች ለመሥራት አሸናፊ በመሆናችሁ እድለኞች ናችሁ፤ የግንባታ ሥራውን በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ በጥራትና በፍጥነት በመሥራት እንድታስረክቡ አደራ እንላለን” ብለዋል።

(የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...

ኧረ ፋታ ስጡን?!

መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው :: አጀንዳ...