ኢትዮጵያና የዓለም ባንክ የ250 ሚ. ዶላር የድጋፍ ስምምነት ተፈራረሙ

Date:

ኢትዮጵያና የዓለም ባንክ ለከተማ ማህበረሰብና ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ የሚውል የ250 ሚሊዮን ዶላር የድጋፍ ስምምነት ተፈራረሙ

የገንዘብ ሚኒስቴር እና ዓለም ባንክ የከተማ ምርታማ ሴፍቲኔትና ስራ እድል ፈጠራ ፕሮጀክትን ለማስፈጸም የሚውል የ250 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ተጨማሪ የገንዘብ ድጋፍ ስምምነት ተፈራርመዋል።

ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰመሬታ ሰዋሰው እና የዓለም ባንክ የኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ ሱዳንና ደቡብ ሱዳን ዳይሬክተር ማርያም ሳሊም ፈርመውታል።

ይህ ተጨማሪ የገንዘብ ድጋፍ የኢትዮጵያ መንግሥት በከተማ የሚኖሩ አነስተኛ ገቢ ያላቸዉን የህብረተሰብ ክፍሎች የኑሮ ሁኔታን ለማሻሻል እንዲሁም ወጣቶችና ሴቶችን በሥራ ገበያው ውስጥ ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመረዉን ስራ አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያግዝ መሆኑን ከገንዘብ ሚኒስቴር ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በ2026 የዓለም ዋንጫ ላይ ለተለያዩ ብሔራዊ ቡድኖች የሚጫወቱ ወንድማማቾች

የ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ከመላው ዓለም የተውጣጡ ምርጥ ተጫዋቾችን...

ኢንፊኒቲ ለቤትና ለመኪና መግዣ ብድር እየሰጠ እንደሚገኝ አስታወቀ

ኢንፊኒቲ ኃላፊነቱ የተወሠነ መሠረታዊ የቁጠባ እና ብድር ኀብረት ሥራ...

የአዲሱ የወንጀል ህግ ስነ-ስርዓት የእርማት ስራዎች ሳይጠናቀቁ በሥራ ላይ እየዋለ ነው

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ላለፉት 64 ዓመታት...

ናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኘ

​የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በሀገሪቱ የካፒታል ገበያ ታሪክ ለመጀመሪያ...