ቱሪዝሙን ለማሳደግ አስቻይ ሁኔታዎችን መፍጠር እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ

Date:

የቱሪዝም ዘረፉን ለማሳደግ እና ለወጣቶች የስራ እድል መፍጠር የሚችል ለማድረግ ለአስጎብኝ ድርጅቶች አስቻይ ሁኔታዎችን መፍጠር እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ፡፡ የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት “በኢትዮጵያ ያለው የቱሪዝም አስጎብኝዎች ዘርፍ እድልና ተግዳሮቶች” ዙሪያ ከኢትዮጵያ አስጎብኝ ድርጅቶች ማህበር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል። የኢትዮጵያ አስጎብኝ ድርጅቶች ማህበር ፕሬዝዳንት አንድነት ፈለቀ ከዚህ ቀደም የቱሪዝም ዘርፍ ብዙም ትኩረት ያልተሰጠው እንደነበር ጠቁመው አሁን ላይ መንግሥት ቱሪዝሙን ለማሳደግና የኢኮኖሚ አቅም እንዲኾን ከማድረግ ጀምሮ ሌሎች እየሰራቸው የሚገኙ ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠል ይኖርባቸውል ብለዋል። ቱሪዝሙን ለማሳደግ እና ለወጣቶች የሥራ እድል መፍጠር የሚችል ለማድረግ ለአስጎብኝ ድርጅቶች አስቻይ ሁኔታዎችን መፍጠር እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል፡፡ በዓለም ዐቀፍ ደረጃ የተከሰተው የኮሮና ቫይረስና የኑሮ ውድነት እንዲሁም በሀገር ውስጥ የተፈጠረው የሰላም መደፍረስ ቱሪዝሙን እንደጎዳው አንስተው መንግሥት ሕጋዊ የኾነውን የአስጎብኝ ድርጅት ለማበረታታት ሕገወጦችን መቆጣጠርና የሚወጡ ሕጎችን ተግባራዊ ማድረግ አለበት ሲሉም ተናግረዋል።

ቀዳሚ ጽሑፍ
ቀጣይ ጥሑፍ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...