ትራምፕ ለኔታንያሁ ማስጠንቀቂያ ሰጡ

Date:

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በሰጡት ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ፣ የእስራኤል ጥቃቶች ወደ እርስ በርስ ሙሉ ጦርነት ከተቀየሩ እስራኤል ያለ አሜሪካ እገዛ ብቻዋን ልትቀር እንደምትችል አስታወቁ።

ትራምፕ ይህንን የተናገሩት ከእስራኤሉ ቻናል 12 ኒውስ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ላይ ሲሆን፣ በመካከለኛው ምስራቅ እየናረ የመጣው ውጥረት ዋሽንግተንን ሊያሳስብ እንደሚችል አመላክተዋል።

ፕሬዚዳንቱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ያስተላለፉትን መልእክት ሲያብራሩ “ለቢቢ (ኔታንያሁ) በምታደርገው ነገር ላይ በጣም ጥንቃቄ ብታደርግ ይሻላል፤ ምክንያቱም በቅርቡ ከኢራን ጋር ብቻህን ልትቀር ትችላለህ ብዬ ነግሬዋለሁ” ማለታቸው ተዘግቧል።

ይህ በትራምፕ እና በኔታንያሁ መካከል የተሰማው ያልተጠበቀ ፍጥጫ፣ በቀጣይ የአሜሪካና የእስራኤል ወታደራዊ ትብብር ላይ ትልቅ ጥያቄ ምልክት ማሳረፉን የፖለቲካ ተንታኞች እየገለጹ ይገኛሉ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...

የብሔር ፌደራሊዝምን ለማስቀጠል “የቆረጡ” ተመካካሪዎች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 14ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች የአጀንዳ...

“የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው” ፓትርያርኩ

የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው...