ቻይና የሱማሊላንድን መገንጠል አልደግፍም ስትል አስታወቀች

Date:

ቻይና ሱማሊላንድ እና ታይዋን እያደረጉት ያሉትን ግንኙነት በፅኑ ተችታለች።

ከቅርብ ግዜያት ወዲህ ተገንጣይ አገራቱ ትብብራቸውን ለማጠናከር እንደሚሰሩ በተለያየ መንገድ ሲገልፁ ነበር።

ይሁንና በሱማሊያ የቻይና አምባሳደር የሆኑት ዋንግ ዩ ፤ ግንኙነታቸውን ተገንጣይነትን ለማስተዋወቅ የተጠነሰሰ ብለውታል።

‹‹በአለም ላይ ያለው አንድ ቻይና ነው፡፡ ታይዋንም የቻይና አንድ አካል ናት፡፡ በርካታ አገራት የቻይናን አንድነት ይደግፋሉ›› ያሉት አምባሳደሩ መሠረታዊው እውነትም ይሄ ነው ብለዋል።

አክለውም የሱማሊያን ሉአላዊ አንድነት ለማስጠበቅ የቤጂንግ መንግስት ከሱማሊያ ፌዴራል መንግስት ጋር በቅርበት እየሰራ እንደሚገኝ ነው የገለፁት ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ዳውድ ኢብሳ ከምርጫው ራሳቸውን አገለሉ

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ በኦሮሚያ...

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ‹‹ሁሉን አቀፍ ስምምነት›› እንደምትፈልግ ገለጸች

ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ጦርነት ለማቆም ከአሜሪካ ጋር በምታደርገው...

የሪል እስቴት ዘርፍ ዘመናዊ የክፍያ ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት አዲስ አጋርነት ፈጠረ

በኢትዮጵያ የሪል እስቴት ዘርፍ ግንባር ቀደም ከሆኑት ድርጅቶች አንዱ...

የአርቲስት ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ

ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ዕድገት ወደር የሌለው አስተዋጽኦ ላበረከተውና የሙዚቃው...