ቼልሲ ማንቼስተር ዩናይትድን አሸነፈ

Date:

በ37ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቼልሲ ማንቼስተር ዩናይትድን 1 ለ ዐ አሸንፏል።

የምዕራብ ለንደኑን ክለብ ቼልሲ ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ማርክ ኩኩሬያ በሁለተኛው አጋማሽ ከመረብ አሳርፏል።

ቼልሲ የምሽቱን ድል ተከትሎ ነጥቡን 66 በማድረስ በኒውካስል ዩናይትድ በግብ ክፍያ ተበልጦ 4ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል።

በውድድር አመቱ በፕሪሚየር ሊጉ ብቻ 18ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ማንቼስተር ዩናይትድ 16ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

ቀደም ብሎ ምሽት 3:30 በተደረገው ጨዋታ አስቶን ቪላ ቶተንሃም ሆትስፐርን 2 ለ 0 በማሸነፍ ለሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎ ወሳኝ 3 ነጥብ አሳክቷል።

የአስቶንቪላን ግቦች ኮንሳ እና ካማራ በሁለተኛው አጋማሽ ከመረብ አሳርፈዋል።

ቪላ ነጥቡን 66 በማድረስ በኒውካስል ዩናይትድና ቼልሲ በግብ ክፍያ ተበልጦ 5ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ፥ ሽንፈት ያስተናገደው ቶተንሃም በነበረበት 17ኛ ደረጃ ላይ ለመቆየት ተገዷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...