ኒውክሌር የታጠቀውን የባህር ኃይል እየገነባች ያለችው ሰሜን ኮሪያ

Date:

የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ኒውክሌር የታጠቀ የባህር ኃይል ለመገንባት የሚያደርጉትን ጥረት የሚደግፍ አዲስ 5 ሺህ ቶን የሚመዝን “ካንግ ኮን” የተባለ የክሩዝ ሚሳኤል እና ሌሎች የጦር መሳሪያዎች ሙከራዎች ላይ ምልከታ ማድረጋቸው ተገለጸ፡፡

እንደ ኮሪያ ማዕከላዊ የዜና ኤጀንሲ ዘገባ፤ ኪም ጆንግ ኡን ስትራቴጂካዊ የመርከብ ሚሳኤል ሙከራን እና ካንግ ኮን የተባለውን ፀረ-ሰርጓጅ መርከብ እና የአየር መከላከያ ስርዓቶችን ገምግመዋል፡፡

ፒዮንግያንግ የኑክሌር ጦር መሳሪያ ለመገንባት የምታደርገውን ጥረት ስትቀጥል የስትራቴጂካዊ የሆኑ ክሩዝ ሚሳኤል ሙከራዎቿን አጠናክራ ቀጥላለች ነው የተባለው፡፡

የሰሜን ኮሪያ መንግስት ለዓመታት የባለስቲክ ሚሳኤል ልማት ላይ ትኩረቱን ካደረገ በኃላ አሁን ላይ የባህር ኃይልን ማደራጀት ላይ አተኩሯል፡፡ በዚህም የኑክሌር ኃይል ያለው ሰርጓጅ መርከቦች ግንባታ ላይ ትኩረቱን አድርጓል ይላል ቲአርቲ ወርልድ በዘገባው፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጉምሩክ ኮሚሽን ከአንድ ትሪሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ማቀዱን ገለጸ

የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን በ2018 በጀት ዓመት 725.25 ቢሊዮን ብር...

ከ1.5 ሚሊዮን ዶላር የአፍሪካ ንፁህ ኢነርጂ ፈንድ አምስቱ አቅኚ የኢትዮጵያ ድርጅቶች ተመረጡ

በምስራቅ አፍሪካ የንፁህ ኢነርጂ አቅርቦትን በማሳደግ የስራ እድልን ለመፍጠርና...

ታላቅ የምስጋና እና የስጦታ መርሃ-ግብር ጥሪ!

ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ባለፉት 5 ዓመታት ላበረከቱት ከፍተኛና ታላቅ...

የቀድሞዉ የኢራን ላዕላይ መሪ አያቶላሕ ዓሊ ኻምኔይ ተቀበሩ

ዩናይትድ ስቴትስና እስራኤል ባለፈዉ የካቲት ማብቂያ ላይ የገደሏቸዉ የኢራን...