የአዲስ አበባ ከተማ ግዙፉ የመጽሐፍ አውደ ርዕይ “ንባብ ለሕይወት ” የመጽሐፍና ንባብ አውደ ርዕይ ከቀናት በኃላ ሊካሄድ እንደሆነ ከአዘጋጆቹ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
“ንባብ ለሕይወት” የመጻሕፍት አውደ ርዕይ ዘንድሮ ከሐምሌ 24 እስከ ሐምሌ 27 2017 ዓ.ም ድረስ ለቀናት መስቀል አደባባይ አካባቢ በሚገኘው በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ውስጥ በታላቅ ድምቀት ይካሄዳል።
የንባብ ከሕይወት ፕሮጀክት ከኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) በመተባባር ባዘጋጀው በዚህ አውደ ርዕይ ላይ በርካታ ደራሲያን በመገኘት መጻሕፋቸውን ያስተዋውቃሉ ተብሏል።
የመጻሕፍት አሳታሚዎችና አከፋፋዮች መጻሕፍትን በቅናሽ ዋጋ ያቀርባሉ።
በአውደ ርዕዩ ላይ የመጽሐፍ ምርቃትና ሀሳብ ማንሸራሸሪያ ልዩ ልዩ መድረኮች ተዘጋጅቷል።
የአውደ ርዕዩ መግቢያ በነፃ ሲሆን ሐሙስ ሐምሌ 24 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:30 ጀምሮ ይከፈታል ተብሏል።
