ኖ ሞር’ ቴአትር በአሜሪካ ለታዳሚ ሊቀርብ ነው

Date:

በአገር ውስጥ መድረኮች በነበረው ቆይታ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈው ‘ኖ ሞር’ (No More) የተሰኘው ቴአትር፣ የባህር ማዶ ጉዞውን በመጀመር በአሜሪካ ዴንቨር ኮሎራዶ ለታዳሚ ሊቀርብ ነው።

ተውኔቱ “በደል የፈፀሙ ሰዎች ተገቢውን ምላሽ ሊያገኙ ይገባል” የሚል ጠንካራ ማህበራዊ መልዕክትን በአስቂኝ ዘውግ አዋህዶ የያዘ ስራ ነው።

ቴአትሩ በኢትዮጵያ ለእይታ በበቃበት ወቅት አራት ተዋንያንን እና ሦስት የቴክኒክ ባለሙያዎችን በማሳተፍ ጥራት ያለው ዝግጅት ማቅረቡ ይታወሳል።

ለኮሎራዶው ዝግጅት በተደረገው ማሻሻያ መሰረት ቴአትሩ የመጀመሪያ ተዋንያን ላይ መጠነኛ ለውጥ ተደርጓል።

‘ኖ ሞር’ በሰው ልጅ ግንኙነት ውስጥ የሚፈጠሩ በደሎችንና ለበደሎቹ የሚሰጡ ምላሾችን በትውፊትና በዘመናዊ የቴአትር አቀራረብ የሚተነትን ነው።

ስራው በዴንቨርና አካባቢው ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የጥበብ ጥምን ለማርካት ታስቦ የተዘጋጀ ሲሆን፥ በቅርቡም የመድረክ ቀኑና የትኬት ሽያጭ ዝርዝር ይፋ እንደሚደረግ ተገልጿል።

ይህ ዝግጅት የኢትዮጵያ ቴአትር ከሀገር ውስጥ አልፎ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያለውን ተቀባይነት ለማሳደግ ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሎ ይታመናል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...