አሜሪካ በኤርትራ የሚገኘውን ጨምሮ 10 ኤምባሲዎቿን ልትዘጋ ነው

Date:

  • ከሚዘጉት ኤምባሲዎች 6ቱ በአፍሪካ የሚገኙ ናቸው ተብሏል

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት በኤርትራና ደቡብ ሱዳን የሚገኙትን ጨምሮ 10 ኤምባሲዎቹን ለመዝጋት ማቀዱ ተገለጸ።

ከኤምባሲዎቹ በተጨማሪ 17 ቆንስላዎቹንም ለመዝጋት ማቀዱን ኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ ዘግቧል።

የውጭ ጉዳይ መ/ቤቱ እንዲዘጉ ባቀዳቸው ኤምባሲዎች ይከናወኑ የነበሩ ስራዎችን በአጎራባች ሀገራት ኤምባሲዎች ለማከናወን ማቀዱንም ዘገባው ጠቁሟቋል።

የኤምባሲዎቹና ቆንስላዎቹ መዘጋት የትራምፕ አስተዳደር የፌደራል መንግሥትን ባጀት ለመቀነስ እየወሰደ ያለው እርምጃ አካል ነው ተብሏል።

አሜሪካ ለመዝጋት ካቀደቻቸው አስር ኤምባሲዎች መካከል ስድስቱ በአፍሪካ የሚገኙ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡

በሶማሊያ ሞቃዲሾ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲም ሙሉ በሙሉ እንዲዘጋ፣ ካልሆነ ደግሞ ሰራተኞቹ በከፍተኛ ቁጥር እንዲቀነሱ ሃሳብ መቅረቡን ዘገባው አመላክቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ዳውድ ኢብሳ ከምርጫው ራሳቸውን አገለሉ

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ በኦሮሚያ...

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ‹‹ሁሉን አቀፍ ስምምነት›› እንደምትፈልግ ገለጸች

ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ጦርነት ለማቆም ከአሜሪካ ጋር በምታደርገው...

የሪል እስቴት ዘርፍ ዘመናዊ የክፍያ ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት አዲስ አጋርነት ፈጠረ

በኢትዮጵያ የሪል እስቴት ዘርፍ ግንባር ቀደም ከሆኑት ድርጅቶች አንዱ...

የአርቲስት ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ

ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ዕድገት ወደር የሌለው አስተዋጽኦ ላበረከተውና የሙዚቃው...