አሜሪካ ኢራንን አጠቃች

Date:


የአሜሪካ ጦር በደቡባዊ ኢራን  አዲስ ጥቃት ሰንዝሯል።

አሜሪካ የሚሳኤል ይዞታዎችን እና ፈንጂ ውሃ ውስጥ ሊያጠምዱ ሲሞክሩ የነበሩ መርከቦችን ዒላማ ማድረጓን አሳውቃለች።

እርምጃ የወሰድንው ራስን ለመከላከል ነው በሚልም ማዕከላዊ ዕዙ ለማስተባበል ሞክሯል።

የኢራን ሀይሎች ስጋት መደቀናቸውን ተከትሎ የተፈፀመ ጥቃት ነው ሴንት ኮም ቢለውም ድርድሩን ጫና ውስጥ ያስገባዋል ተብሏል።

የኢራን ፖለቲከኞች ድርድሮች በበጎ እየቀጠሉ ነው ባሉበት ሰዓት የተሰነዘረ ጥቃት በመሆኑ ቴህራንም ተመሳሳይ እርምጃ ልትወስድ ትችላለች የሚል ስጋት ተጋርጧል።

እንደ ኒው ዮርክ ታይምስ ዘገባ ጥቃቱ በባንዳር አባስ አቅራቢያ ተፈፅሟል።

በሌላ በኩል በሊባኖሱ ሄዝቦላህ ላይ የእስራኤል ጥቃት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ማሳወቃቸው ውጥረቱ አደገኛ እየሆነ መምጣቱን ይጠቁማል ተብሏል።

ዜናው እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረሰ ከኢራን በኩል የተሰጠ ምላሽ አለመኖሩም ተዘግቧል።

ኒው ዮርክ ታይምስና አልጀዚራ እንዳስነበቡት።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በቬንዝዌላ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ የ32 ሰዎች ህይወት አልፏል

በቬንዙዌላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን 7.2 እና 7.5...

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ “ሉሲ” ላገኟት ፕሮፌሰር የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጠ

የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ፥...

የሳህለወርቅ ዘውዴ አዲሱ አለም አቀፍ ሹመት በተመድ ልዩ ተልእኮ ተሰጣቸው

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተመድ ዋና ፀሀፊ...

በሳዑዲ በምሕረት የተለቀቁ 320 ኢትዮጵያውያን

በሳዑዲ አረቢያ የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምህረት አዋጅ ከተሰጣቸው 1...