አሜሪካ ዜጎቿ ከ14 አገራት በአስቸኳይ እንዲወጡ አዘዘች

Date:

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዜጎቹ በመካከለኛው ምሥራቅ ከሚገኙ 14 አገራት በአስቸኳይ ለቅቀው እንዲወጡ አዘዘ።

የአገሪቱ የቆንስላ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስቴር የሆኑት ሞራ ናምዳር በመሥሪያ ቤታቸው የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ ባሰፈሩት መልዕክት አሜሪካውያን “ሊያጋጥሙ በሚችሉ ከባድ አደጋዎች ምክንያት” ከአስራ አራቱ አገራት “ያሉ የትራንስፖርት አመራጮችን በመጠቀም አሁኑኑ” ለቅቀው እንዲወጡ አሳስበዋል።

የአሜሪካ ዜጎች በአስቸኳይ ለቅቀው እንዲወጡ የታዘዙባቸው አገራት ባህሬን፣ ግብፅ፣ ኢራን፣ ኢራቅ፣ እስራኤል፣ የፍልስጤም ግዛቶች፣ ዮርዳኖስ፣ ኩዌት፣ ሊባኖስ፣ ኦማን፣ ኳታር፣ ሳዑዲ አረቢያ፣ ሶሪያ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እና የመን ይገኙባቸዋል።

በኩዌት የሚገኘው ኤምባሲ ለየትኛውም የቆስንስላ ጉዳዮች የሚሰጠውን አገልግሎት ማቋረጡን ማስታወቁ ይታወሳል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚያደርጉት ድርድር እስኪጠናቀቅ ድረስ የተኩስ አቁሙ መራዘሙን አስታወቁ

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፓኪስታን ጥያቄ መሠረት ከኢራን ጋር የገቡትንየተኩስ...

ለኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ የሚውል የ40 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ተፈቀደ

የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የልማት ክንፍ የሆነው ኢአይቢ ግሎባል (EIB...

ሃይንከን በአልኮል መጠኑ ጠንከር ያለ ቢራ ለኢትዮጵያ ገበያ አስተዋወቀ

ሃይንከን ኢትዮጵያ በእለም አቀፍ ደረጃ ዝነኛ የሆነውን ዴሰፔራዶስ (Desperados)...