አሜሪካ ዜጎቿ ከ14 አገራት በአስቸኳይ እንዲወጡ አዘዘች

Date:

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዜጎቹ በመካከለኛው ምሥራቅ ከሚገኙ 14 አገራት በአስቸኳይ ለቅቀው እንዲወጡ አዘዘ።

የአገሪቱ የቆንስላ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስቴር የሆኑት ሞራ ናምዳር በመሥሪያ ቤታቸው የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ ባሰፈሩት መልዕክት አሜሪካውያን “ሊያጋጥሙ በሚችሉ ከባድ አደጋዎች ምክንያት” ከአስራ አራቱ አገራት “ያሉ የትራንስፖርት አመራጮችን በመጠቀም አሁኑኑ” ለቅቀው እንዲወጡ አሳስበዋል።

የአሜሪካ ዜጎች በአስቸኳይ ለቅቀው እንዲወጡ የታዘዙባቸው አገራት ባህሬን፣ ግብፅ፣ ኢራን፣ ኢራቅ፣ እስራኤል፣ የፍልስጤም ግዛቶች፣ ዮርዳኖስ፣ ኩዌት፣ ሊባኖስ፣ ኦማን፣ ኳታር፣ ሳዑዲ አረቢያ፣ ሶሪያ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እና የመን ይገኙባቸዋል።

በኩዌት የሚገኘው ኤምባሲ ለየትኛውም የቆስንስላ ጉዳዮች የሚሰጠውን አገልግሎት ማቋረጡን ማስታወቁ ይታወሳል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በአንድ ዓመት ውስጥ ቃል የተገቡ 417 የዓይን ብሌኖች ለሆስፒታሎች ተሰራጩ

​ የኢትዮጵያ የደምና ሕብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት በተጠናቀቀው የ2018 በጀት...

በኢትዮጵያ በውርስና ስጦታ ላይ አዲስ ታክስ ሊጣል ነው

በኢትዮጵያ በውርስና ስጦታ ላይ አዲስ ታክስ ሊጣል ነው በኢትዮጵያ...

ትምህርት ሚኒስቴር ለአዲሱ ዓመት 11 አዳዲስ የሙያ ትምህርት ዓይነቶችን ይፋ አደረገ

​የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ከክልል...

የአዲስ አበባ ጉዳይ በሌሎች አጀንዳዎች ላይ የሚካሄደውን ምክክር ጥላ አጥሎበታል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በ25ኛ ቀን ውሎው በሥራ ቡድን ደረጃ...