አፍሪካ የኃይል ችግርን ለመፍታት 50 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል

Date:

አፍሪካ በ2030 ለሁሉም ዜጎቿ የኃይል አቅርቦትን ለማረጋገጥ በየዓመቱ ከ25 እስከ 50 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልጋት ተዘግቧል ። ይህ መጠን የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ከሚያስፈልገው ተጨማሪ 200 ቢሊዮን ዶላር ጋር ተደምሮ የአህጉሪቱን የፋይናንስ ጫና እጅግ ከፍ ያደርገዋል።

በአሁኑ ወቅት የአየር ንብረት ፋይናንስ አወቃቀር ለዕርዳታ ሳይሆን ለብድር ቅድሚያ መስጠቱ ለአፍሪካ አገሮች አዲስ የዕዳ ጫና እየፈጠረ ነው። ይህ ሁኔታ አህጉሪቱ ቀደም ሲል ከነበረባት ከባድ የዕዳ ሸክም በተጨማሪ ተጨማሪ ብድር እንድትወስድ ይገፋፋታል።

ባለሙያዎች እንደሚሉት፣ ይህ አካሄድ አፍሪካን ወደ ጥልቅ የጥገኝነት ወጥመድ ሊያስገባት ይችላል።

የተባበሩት መንግስታት ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮ ሀብቶች ተቋም (UNU-INRA) ያወጣው ሪፖርት እንዳመለከተው ፤ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀነስ ብዙ ልቀት የሚያመነጩ ሀገሮች ፍትሃዊ የሆነ ድርሻቸውን ሳይወጡ፣ አፍሪካ ብቻዋን የሌሎችን የአየር ንብረት ምኞት ለማሳካት እየተገደደች፣ ወደ የከፋ የኃይል ድህነት ልትገባ እንደምትችል አመልክቷል።

አፍሪካ ለዓለም አቀፍ ልቀት አስተዋጽኦ ያደረገችው እምብዛም ባይሆንም፣ የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ተጽዕኖ እያሳደረባት ነው። የአየር ንብረት ለውጡ በከተሞች ላይ ጉዳት ከማድረሱም በላይ የምግብ ዋስትና እጥረትን እያባባሰ መሆኑንም ተጠቁሟል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...