ኢራን የእስራኤል የስለላ ድርጅት ‘ሞሳድ’ ዋና መስሪያ ቤትን በሚሳኤል መምታቷን የኢራን መንግሥታዊ ሚዲያ ታስኒም የዜና ወኪል ዘገበ።
የዜና ወኪሉ የአገሪቱን አብዮታዊ ብሔራዊ ዘብ ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው የሞሳድ ቢሮ በኢራን ሚሳኤሎች መመታቱን ገልጿል።
ታስኒም የሞሳድ መስሪያ ቤት እንደሆኑ የገለጻቸው ህንጻው በእሳት ተያይዞ የሚያሳዩ ፎቶዎችን አጋርቷል።
“የኢራን አብዮታዊ ብሔራዊ ዘብ የኤሮስፔስ ተዋጊዎች ከፍተኛ ውጤት ለማምጣት ባነጣጠረ ዘመቻ ምንም እንኳን ከፍተኛ የላቁ የመከላከያ ስርዓቶች ቢዘረጉም የወታደራዊ ስለላ ማዕከሉን መትተዋል” ሲል የዜና ወኪሉ በቴሌግራም ገጹ አጋርቷል።
እስራኤል በሞሳድ ላይ ስለተፈጸመው የሚሳኤል ጥቃት ያለችው ነገር የለም።
የእስራኤል መንግሥት በጣለባቸው እገዳዎች ምክንያት አንዳንድ በጥቃቱ ኢላማ የተደረጉ ስፍራዎችን በተመለከተ የአገሪቱ ሚዲያዎች ሊዘግቡ አይችሉም።
