ኢሰመኮ መንግሥት አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድ አሳሰበ

Date:

​በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች ውስጥ በንጹሃን ዜጎች ላይ እየተፈጸመ ያለው ግድያ፣ እገታና መፈናቀል በአሳሳቢ ሁኔታ መቀጠሉን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ።

ኮሚሽኑ ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ በተለይም ከጥቅምት 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በሽርካ፣ በጉና፣ በመርቲ እና በሌሎች የአርሲ ዞን አካባቢዎች የታጠቁ ኃይሎች በሰነዘሩት ተደጋጋሚ ጥቃት ሳቢያ የሰው ሕይወት መጥፋቱን፣ የአካል ጉዳት መድረሱንና መጠነ ሰፊ የንብረት ውድመት መከሰቱን ገልጿል።

የግጭቱ መባባስ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎችን ለስደት የዳረገ ሲሆን፣ የካቲት 19 ቀን በሽርካ እና ሮቤ ወረዳዎች በንጹሃን ላይ የተፈጸመው ግድያና እገታ የችግሩን አስከፊነት አጉልቶ አሳይቷል።

የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ መንግሥት የዜጎችን ደህንነት የማስከበር ሕገ-መንግሥታዊ ግዴታውን እንዲወጣና በአካባቢው በቂ የጸጥታ ኃይል እንዲያሰማራ ጥሪ አቅርበዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...