ኢትዮጵያ ባለፉት 6 ዓመታት ዓለማቀፍ የልማት ግቦችን እያሳካች እንደሆነ ተነገረ

Date:

አፈ ጉባኤው ኡዝቤኪስታን በሚካሄደው 150ኛ ዓለማቀፍ የፓርላማ ሕብረት ጉባኤ ላይ ተሳትፎ እያደረጉ ነው፡፡

አፈ ጉባኤው አገኘሁ ተሻገር በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ከ2030 የዘላቂ ልማት ግቦች እና ከአፍሪካ አጀንዳ 2063 ጋር የተጣጣመ የአሥር ዓመት ሀገራዊ የልማት ዕቅድ አውጥታ እየሠራች እንደምትገኝ አብራርተዋል።

ባለፉት ስድስት ዓመታት ዓለም አቀፍ የልማት ግቦችን በማሳካት ረገድ ከፍተኛ ውጤት እያሳየች እንዲሁም ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገበች እንደሆነም በንግግራቸው ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፓርላማ የሚሊኒየሙን የዘላቂ ልማት ግቦች ለማሳካት የተለያዩ ፖሊሲዎች፣ ፕሮግራሞችና የሕግ ማዕቀፎችን መርምሮ በማፅደቅ፣ ክትትልና ድግፍ በማድረግ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እየተወጣ ይገኛል ማለታቸውን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አስታውቋል፡፡

@sputnik_ethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ12ኛ ክፍል ተፈታኞች  565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አላሳለፉም

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በተመዘገበው ውጤት...

የአማርኛ ቋንቋ እውነተኛ ምንጭ ቤተ መንግሥት ሳይሆን ሕዝብና ሠራዊት ነው

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋ ማበልጸጊያ ተቋም አዘጋጅነት ከስድስት...

አዲስ አበባ፦ የዜጎች ቀይ መስመር!

(የግል አስተያየት) አዲስ አበባ የኢትዮጵያውያን መናገሻ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህሎች ለዘመናት...

አብን የምክክሩን ውጤት ውድቅ አደረገ!

አብን በሀገራዊ ምክክሩ ማጠቃለያ ላይ የተፈጸመውን “ሕገ-ወጥ ጣልቃ-ገብነት” በመቃወም...