በቴሌኮም ዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ማጭበርበሮችን የብሔራዊ መታወቂያን በመጠቀም ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ እንዳሉ ተገለፀ

Date:

በበርካታ ዘርፎች እንደ ቅድመ ሁኔታ እየተጠየቀ የሚገኘው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በቀጣይም በቴሌኮም ዘርፉ ላይ ማጭበርበሮችን ለመከላከል በሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ ተግባራዊ ለማድረግ ስራዎች መጀመራቸውን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታውቋል።

በቅድመ ሁኔታ ተግባራዊ ሲደረግም የሲም ካርድ ቁጥጥር እና ያለአግባብ በሲም ካርዶች የሚፈፀሙ የብድር ማጭበርበሮችን ለማስቀረት እንደሚረዳ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የባለድርሻ አካላት ዳይሬክተር አቶ ሳሚናስ በላይነህ ተናግረዋል።

የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አንድ ማንነትን ለአንድ ግለሰብ የሚሰጥ በመሆኑ በአገልግሎት ሰጪ ማዕከላት ላይ የነበረውን ክፍተት ለመሙላት እንደሚያግዝ እና ተቋማትን እንደሚያስተሳስርም ሃላፊው አንስተዋል።

እንዲሁም በትምህርት፣ በፋይናንስ እና በአገልግሎት መስጫ ተቋማት ላይ ተግባራዊ የሚደረገው ፋይዳ ነባር መታወቂያዎችን ተክቶ የሚያስቀር እንዳልሆነ አቶ ሳሚናስ ገልፀዋል ።

እስካሁን ባለውም በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ13 ሚሊየን በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ለማግኘት መመዝገባቸውን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የእግር ኳስ ዳኝነት በኢትዮጵያ

ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) ግዮን መጽሔት :- እግር ኳስ...

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...