ኢትዮጵያ ከዓለም ምርጥ ስንዴ አምራች ሀገራት 20ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች

Date:

የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር በመተባበር በዛሬው ዕለት “ከራዕይ ወደ ተግባር የኢትዮጵያ ዘላቂና አካታች የምግብ ስርዓት ሽግግር ጉዞ” በሚል መሪ ሀሳብ የፓናል ውይይት አድርጓል፡፡

በፓናል ውይይቱ የግብርና ባለሙያዎች፣ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን፣ ጋዜጠኞች፣ የክልሎች ግብርና ቢሮ አመራሮች ተሳትፈዋል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮ ሳይንስ እና ቀመር ኮሌጅ ዲን ቢቂላ ወርቅነህ (ዶ/ር) በፓናል ውይይቱ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በስንዴ አምራችነት ከዓለም 20ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።

ሆኖም በስንዴ ምርት ከዓለም ምርጥ አምስት አምራች ሀገራት ውስጥ ሊያስገባ የሚችል አቅም አላት ብለዋል፡፡

እንደ ዶክተሩ ገለጻ፤ ኢትዮጵያ መሰል ምርቶቿን ለማሳደግ የአረንጓዴ አሻራ ሥራዎችን አጠናክራ እየሠራች ትገኛለች።

በምርታማነት ላይ ተግዳሮቶችን የሚደቅኑ እንደ አየር ንብረት ለውጥ አይነት ፈተናዎች ሊቀረፉ የሚችሉት በአረንጓዴ አሻራ መሆኑን ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የምታበረክተው 0.02 በመቶ ብቻ መሆኑን ጠቅሰው፤ የአየር ንብረት ለውጡ የሚመጣው ያደጉ ሀገራት በሚለቁት በካይ ጋዝ ሆኖ፣ በአየር ንብረት ለውጥ ኢትዮጵያ ትፈተናለች ብለዋል።

ኢትዮጵያ እንደሀገር ይሄንን በመረዳት አረንጓዴ አሻራ የሚል መርሀግብር አስጀምራ በዚህ ንቅናቄም የደን ሽፋንን በመጨመር ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርናን ዘርፍ ለመገንባት እየሰራች እንደሆነ ተናግረዋል።

ይህም የምርታማነት አቅሟን የሚያሳድግ እንደሆነ አስረድተዋል።

ጋዜጣ_ፕላስ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...