ኢትዮጵያዊቷ ሴት መካኒክ የተባበሩት መንግሥታት የክብር ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኑ

Date:

በደቡብ ሱዳን የተባበሩት መንግሥታት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ውስጥ በመካኒክነት በማገልገል ላይ የሚገኙት ሻለቃ ትዕግስት ፈረደ፤ በተለምዶ የወንድ ሥራ ተብሎ በሚቆጠረው ሙያ ላበረከቱት ላቅ ያለ አስተዋጽኦ የክብር ሜዳሊያ ተሸልመዋል።

በምዕራብ ኢኳቶሪያ (ያምቢዮ) በተሠማራው የኢትዮጵያ ሰላም አሰከባሪ ኃይል አባል የሆኑት ሻለቃ ትዕግስት፤ የሰላም አስከባሪ ተሽከርካሪዎች ሁልጊዜ ለተልዕኮ ዝግጁ እንዲሆኑ በማድረግ ረገድ ቁልፍ ሚና በመጫወታቸው ነው እውቅናውን ያገኙት፡፡

“ሁሉም የምጠግናቸው ተሽከርካሪዎች ተስፋን ይሰንቃሉ። ደህንነታቸው ተጠብቆ ሲንቀሳቀሱ ለሰላም የበኩሌን እንደተወጣሁ ይሰማኛል። ይህንን ሜዳሊያ በማጥለቄ በሰላም ማስከበር ሥራ ውስጥ ትንሽ የሚባል ሚና እንደሌለ ተገንዝቤያለሁ” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ ከ20 ዓመታት በላይ ያገለገሉ ሲሆን ከደቡብ ሱዳን በፊት የመጀመሪያ ዓለም አቀፍ የሰላም ማስከበር ተልዕኳቸውን በሱዳን ተወጥተዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...