ኤምባሲዎችና የውጭ ባለሀብቶች በ«ፍራንኮ-ቫሉታ» ነዳጅ እንዲያስገቡ ተፈቀደ

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ኤምባሲዎች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና የውጭ ቀጥተኛ ባለሀብቶች በራሳቸው የውጭ ምንዛሬ (በፍራንኮ-ቫሉታ) ነዳጅ እንዲያስገቡ የሚፈቅደውን አዲስ መመሪያ ተግባራዊ አድርጓል።

በማዕከላዊ ገዢው እዮብ ተካልኝ ፊርማ ባለፈዉ ሳምንት የጸደቀው ይህ መመሪያ፣ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ፍላጎት በማቃለል የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን ለመፍጠር ያለመ ሲሆን፤ የሚገባው ነዳጅ ለተቋማቱ የራስ አገልግሎት ብቻ እንዲውል፣ ለንግድ እንዳይቀርብ እና በዲጂታል ሥርዓት በጥብቅ እንዲከታተል ይደነግጋል።

ባለፉት ዓመታት የነዳጅ ምርቶችን ወደ ሀገር ውስጥ በብቸኝነት የማስገባት መብት የነበረው የመንግሥት ይዞታ ለሆነው ለኢትዮጵያ የነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ነበር። ይሁን እንጂ ነዳጅ የሀገሪቱ ትልቁ የገቢ ምርት መሆኑ እና የውጭ ምንዛሬ እጥረት መኖሩ አቅርቦቱ ላይ ተጽዕኖ ፈጥሮ ቆይቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...

የብሔር ፌደራሊዝምን ለማስቀጠል “የቆረጡ” ተመካካሪዎች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 14ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች የአጀንዳ...

“የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው” ፓትርያርኩ

የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው...