“ከትራምፕ ጋር አንተባበርም” ቺካጎ

Date:

የቺካጎ ከንቲባ የዶናልድ ትራምፕን ውሳኔ በመቃወም የከተማዋ ፖሊስ ከብሄራዊ ዘቡ ጋር እንዳይተባበር አዘዙ።

የፌደራሉን መንግስት ጣልቃ ገብነት አግባብነት የሌለው ነው ያሉት ከንቲባው መተባበር አያሻንም፤ በራሳችን መወጣት የምንችለውን ጉዳይ ብሄራዊ ዘብ ሀይል ማስፈር ትርጉም የለውም ብለዋል።

የቺካጎ ከንቲባ ብራንዶን ጆንሰን ትራምፕን የተቃወመ ትዕዛዝ ሰተዋል፤ ፊርማቸውንም አሳርፈዋል።

ፖሊስ ከየትኞቹም የፌደራል ሀይሎች ጋር ትብብር እንዳይኖረው የሚከለክለው ውሳኔ ምናልባትም በአሜሪካ ተጨማሪ አለመረጋጋትን እንዳይፈጥር ስጋት ጋርጧል።

ሪፐብሊካኑ ትራምፕ በሚቀጥሉት ቀናት ውስጥ ብሄራዊ ዘቡን ወደ ቺካጎ ሊልኩ እንደሚችሉ እየተነገረ ነው።

ዴሞክራቱ ከንቲባ ጆንሰን ደግሞ ይህን ውሳኔ መቃወማቸው እና አንተባበርም የሚል አቋም ላይ መድረሳቸው በሁለቱ ፓርቲዎች መካከል ፖለቲካዊ እሰጥ አገባው እየበረታ መሄዱን የሚያሳይ ያደርገዋል።

ዶናልድ ትራምፕ በሎስ አንጀለስና ዋሽንግተን ዲሲ ብሄራዊ ዘብ አስፍረው ከተሞችን ተቆጣጥረዋል በሚልም በዴሞክራቶቹ እየተወቀሱ ነው።

ትራምፕ ዴሞክራት ከንቲባዎች በሚያስተዳድሯቸው ከተሞች ላይ ትኩረት አድርገዋል ቢባሉም ከተሞቹን ከወንጀል ነጻ ለማድረግ አማራጩ ይህ ነው ብለውታል።

ከተሞቹ እየሰሩ ያለውን ስራ ግምት ውስጥ ሳያስገባ እንዲሁም ስጋት በሌለበት አጋጣሚ ብሄራዊ ዘቡን ትራምፕ አሰማርተዋል ይላሉ ዴሞክራቶ ሲል ኤን ቢ ሲ ኢንዲያ ቱዴይን ዋቢ በማድረግ ዘግቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...