ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ክብርት ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ ከጌትስ ፋውንዴሽን የኢትዮጵያ ፕሮግራም ዳይሬክተር ከሆኑት ዶክተር አበበ ቸኮል ጋር ባደረጉት ውይይት፣ የሴት አመራሮች ስልጠና ፕሮግራም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተስማምተዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ጾታን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶችን ለመከላከል፣ ሴቶችን በኢኮኖሚ ለማብቃትና በሴቶችና ህጻናት ላይ የሚፈጸሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለማስቀረት በሚኒስቴሩ የሚከናወኑ ተግባራትን ፋውንዴሽኑ በቁርጠኝነት ለመደገፍ ቃል ገብቷል።
ይህ ትብብር የኢትዮጵያውያን ሴቶችን ህይወት በመለወጥ ረገድ ትልቅ ሚና እንደሚኖረውም በውይይቱ ተመላክቷል።
